tirsdag 29. juli 2014

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሕወሓት መንግስት በአንዳርጋቸው ላይ ላወጣው ቪዲዮ ምላሽ ሰጡ

የግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሕወሓት መንግስት ከ3 ቀን በፊት በቲቪ በማሳየት ላቀረበው ቪድዮ ምላሽ ሰጡ። ቪድዮው የተዘጋጀው የሰውን አንገት ለማስደፋትና ለፕሮፓጋንዳ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ብርሃኑ በአቶ አንዳርጋቸው እጅ ምንም ዓይነት ምስጢሮች እንደሌሎ ተናግረዋል። አቶ አንዳርጋቸው ሰጥተውታል ለተባለው ፓስወርድም “የኦፕሬሽናል ጉዳዮችን የያዘ ፓስወርድ አይደለም፤” ያሉት ዶ/ር አንዳርጋቸው የሰጠው ፓስወርድ የተለያዩ ጥናቶችን የያዘ እንጂ ወያኔ ቢያገኘውም ባያገኘውም ምንም የሚጎዳ ነገር አይደለም ብለዋል። ዶ/ሩ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር በኢሳት ቲቪ የተነጋገሩበት ቪድዮ ይኸው።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar