tirsdag 20. mai 2014

በቡራዩ ከተነሳው ተቃውሞ ጋር አሁንም በርካታ ወጣቶች ታስረው እንደሚገኙ ታወቀ

ግንቦት ፲፪ (አስራ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ አዲሱ ካርታ ጋር በተያያዘ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ በቡራዩ ከታሰሩት ከ200 በላይ ወጣቶች መካከል ከ40 በላይ የሚሆኑት አሁንም ታስረው ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን የእስር ቤት ምንጮች ገልጸዋል።

አብዛኞቹ በ25 ሺ ብር ዋስ ወይም በቦታ ካርታ እንዲፈቱ ቢደረግም ገንዘብ መክፈል ያልቻሉትና ከኦነግ ጋር ግንኙነት ያላቸው ተብለው የተጠረጠሩት እንዳይፈቱ ተደርጓል። እስረኞቹ ፍርድ ቤት ሳይቀረቡ በፖሊስ ዋስ ብቻ 25 ሺ ብር እየከፈሉ እንዲወጡ መደረጉ ግልጽ ዘረፋ መሆኑን አንዳንድ ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጸዋል።
በእስር ላይ ከሚገኙት 6 ሴቶች መካከል አያንቱ የምትባለዋ ወጣት እጆቿ በድብደባ መሰባበሩንና በከፍተኛ ህመም ላይ እንደምትገኝ ታውቋል።
ጋዲሳ እና ዳውድ ሃሰን የተባሉት እስረኞች በኦነግ አባልነት በመጠርጠራቸው በዋስ እንዳይፈቱ ተደርጓል።
ጆቴ፣ ስራታ እና ስሮንሳ ፋይሳ ደግሞ የአዋሽ ባንክ ሰራተኞች ሲሆኑ እነሱም በእስር ቤት ውስጥ ከፍተኛ ስቃይ እየተፈጸመባቸው ነው። ጋዲሳ የተባለው የመንግስት ሰራተኛም ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል ይጠቀሳል።
ንጉማ፣ ወጋሪ፣ ኡመድ ኡመርና ዳባ ቱፋ የተባሉትም እንዲሁ ከፍተኛ ድብደባ የተፈጸመባቸው በመሆኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
በክልሉ ውስጥ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ተይዘው የታሰሩ ሲሆን አንዳንዶች በገንዘብ ዋስ ሲለቀቁ በርካቶች አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ።
በሌላ ዜና ደግሞ በምስራቅና ምእራብ ወለጋ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች የሌሎችን ብሄር ሰዎች እያሰቃዩ መሆኑን ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች ያመለክታሉ።
በወረዳና በዞን ደረጃ የሚሰሩ የኦህዴድ ሹሞች የሌሎች አካባቢ ተወላጆችን አቤቱታ እና ችግር ለማየት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ፣ የሌሎች አካባቢ ነዋሪዎች ለከፍተኛ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሆን ተብሎ እንደተቀናበረ በሚያሳይ መልኩ የተደራጁ ወጣቶች ማታ ማታ በሌሎች አካባቢ ተወላጆች ቤቶች ላይ ጉዳት ሲያደርጉ ሰንብተዋል።
ኢሳት ያነጋገራቸው ሰዎች እንደሚሉት የኦህዴድ ባለስልጣናት በሚዲያ ቀርበው የሚናገሩትና በተግባር እየፈጸሙ ያሉት ድርጊት የተለያየ ነው።
ህወሃት ብሄሮችን እርስ በርስ በማጋጨት በአገር ውስጥ የገጠመውን አስተዳደራዊ ችግር አቅጣጫ ለማስቀየር እየሞከረ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።

Detained Journalists and Bloggers in Ethiopia Must be Charged or Released, says IFJ

May 20, 2014
(reliefweb) – The International Federation of Journalists (IFJ) has today severely criticised authorities in Ethiopia following the decision by a court to grant police nearly one more month to conduct investigations against the journalists and bloggers detained in the country last month.Free Detained Journalists and Bloggers in Ethiopia
Three journalists and six bloggers were arrested on 25 and 26 April by police using an arrest warrant from a public prosecutor in Addis Ababa, the country’s capital city. The police on May 17 said that while the investigations continue the three journalists and six bloggers will remain in prison.
“This is a clear human right violation,” said Gabriel Baglo, IFJ Africa Director. “These journalists and bloggers have not been charged yet and must be released immediately. The court is clearly hesitating because there are no strong charges against our colleagues”.
The IFJ criticism comes a few weeks after it wrote an open letter to U.S. Secretary of State, John Kerry, during his visit to the country to ask him to raise his concerns about the ordeal of the imprisoned journalists when he met with Ethiopian Prime Minister, Hailemariam Desalegn.
According to media reports, Kerry subsequently raised the arrests during meetings with the Prime Minister and Foreign Minister, Tedros Adhanom, on May 1. Following the meeting the IFJ welcomed Kerry’s action, but the Ethiopian court has now taken the decision to extend their detention.
The journalists who have been arrested are Tesfalem Weldeyest, who writes independent commentary on political issues for Ethiopia’s Addis Standard magazine and Addis Fortune newspaper, Asmamaw Hailegiorgis, senior editor at an influential Amharic weekly magazine Addis Guday, and Edom Kassaye, who previously worked at state daily Addis Zemen Newspaper and is an active member of the Ethiopian Environmental Journalists Association (EEJA).
The bloggers are reportedly members of the Zone 9 group, which is known to be very critical of government policy. They have a strong following on social media. They are: Atnaf Berahane, Befeqadu Hailu, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Abel Wabela and Zelalem Kiberet. They are accused of using social media to create instability in the country and collaborating with international human rights organizations.
According to independent news reports, Ethiopian police said on Saturday, May 17, that the detainees were to be charged with the country’s anti-terrorism proclamation, No 652, published on 28 August 2009, which violates international standards on freedom of expression.
The IFJ believes that this proclamation directly threatens freedom of expression and human rights in the country which is Africa’s second worst jailer of journalists and media professionals.
Independent sources have reported that at least three of the detainees have complained of severe torture and long interrogations, while they have only seen their lawyers twice since their arrests.
“Holding detainees without charge for a prolonged period is a new trend that is becoming routine and systematic,” said Baglo. “It is another severe blow to human rights in Ethiopia and the international community must stand up and fight against it.”

søndag 18. mai 2014

ግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል ላለፉት ሶስት ወራት ያሰለጠናቸውን የአራተኛ ዙር ታጋዮችን አስመረቀ


May 18, 2014
የኢትዮጵያዊያንን ስቃይና መከራ ሊያቅብና እንባቸውን ሊየብስ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጎጠኛው ሕወሃት የደረሰባትንና እየደረሰባት ያለውን ውርደት ወደ ክብር ለመለወጥና የናቋትና ያዋረዷት በፍትህ ሚዛን ላይ እንዲቀመጡና ፍርዳቸውን እንዲያገኙ ለማድረግ ዓላማየ ብሎ ምሎ ዱሩ ቤቴ ካለ ገና ሁለት ዓመት እንኳ ያልሞላው ግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል በቃሉ መሰረት አራተኛውን ዙር የታጋዮች የምረቃ በአል ሚያዚያ 26 2006 ዓ/ም ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት ማክበሩን አስታወቀ። ይህ የአራተኛው ዙር ስልጠና በሰልጣኞች ቁጥርም ሆነ በስልጠናው ጥንካሬ ካለፉት ሶስት ዙሮች በእጅጉ የተለየ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን በአሁኑ ሰአት ያለውን የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበና ወቅቱ የሚፈልገውን ቴክኖሎጅ በመጠቀም መረጃን መቀበልና ማስተላለፍን የጨመረም እንደነበር ተያይዞ ተጠቅሷል።Ginbot 7 Popular Force - GPF formed
በሀገር ውስጥ ፋሽስት ወያኔ እያደረሰው ባለው መረን የወጣ ግፍ የተበሳጩና ሁሉም ልክ እንዳለው ለማሳየት ቆርጠው የተሰለፉት እነዚህ ምሩቅ ታጋዮች ከወታደራዊው ስልጠና በተጨማሪ የፖለቲካ፣ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ሌሎችንም ተያያዥ ክህሎቶችን በበቂ ሁኔታ እንደቀሰሙም ተጠቁሟል። ስልጠናው ታጋዮቹ ወደፊት ከሚያጋጥማቸው ጠንካራ ፈተናና ከሚሰለፉበት ጥብቅ ግዳጅ አንጻር በቀላሉ ተስፋ እንዳይቆርጡ ለማድረግ በአካልም ሆነ በመንፈስ ዝግጁ እንደሚያደርጋቸው የተገለጸ ሲሆን የተጀመረው ሕዝባዊ ትግል በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን በጋራና በተቀነባበረ ሃይል ለድል እንደሚበቃና ይህን የጋራ ሃይል በጠነካራ እጆች ላይ ላመስቀመጥም የተሰጠው ስልጠና ከበቂ በላይ ነበር ተብሏል።
ግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል በሀገር ውስጥ እንደማእበል እየገነፈለ ያለውን የአታግሉን የሕዝብ ጣያቄ በተደራጀና በተቀነባበረ መንገድ በተገቢው መልኩ ለማስተናገድ እንዲችል እንደ ድርጅት ከመቼው በላይ ራሱን እያደራጀና እያጠነከረ እንደሚገኝና ምቹ አታጋይ ተቋም ሆኖ ለመውጣት ሌት ተቀን እየደከመ መሆኑም ተያይዞ ተጠቅሷል። በታጋዮች ስልጠና ወቅት የተገኙ አንዳንድ የክብር እንግዶች እንደጠቆሙትም ”ባሁኑ ሰአት በሀገር ውስጥ ያለው ሁኔታ ከመቼውም በላይ የተመቻቸ ነው” ካሉ በሗላ ”ሕወሃት የሚተማመንበት ወታደሩ እንኳ ቁጥሩ ካልሆነ በቀር ልቡም ሆነ መንፈሱ ከሕዝብ ጋር ነው፤ በሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች እየሆነ ያለው ወያኔ በእርጅና ዘምኑ ማብቂያ ላይ መሆኑን ነው የሚያመለክተው። ስለሆነም በመረጃ መንቀሳቀስና በትብብር መስራት ባጭሩ ለድል ያበቃል። ለዚህ ደግሞ የዛሬ ምሩቅ ታጋዮች ያገኙት ስልጠና ለታሰበው ስኬት የሚያበቃቸው ነው” በማለት ትዝብታቸውን አጠቃለዋል።
በምረቃው ማብቂያ ላይ ራሱን ግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል ብሎ ከሰየመበት ጊዜ ጀምሮ ለፋሽስት ወያኔ ከፍተኛ ስጋት እንደሆነ በማስረገጥ የጠቆሙት የሕዝባዊ ሃይሉ ሃላፊዎች፤ ከዚህ በፊት ፋሽስት ወያኔ በከፍተኛ ወጭና ጥንቃቄ ሕዝባዊ ሃይሉን ለማፈራረስና ለማትፋት በከፍተኛ ሁኔታ የሰራ ቢሆንም በሕዝባዊ ሃይሉ መረጃና ደህንነት ክፍል መክሸፉን አስታውሰው፤ ዓላማችንን ከዳር ለማድረስና የሕዝባችንን አርነት ለመመለስ ሀገራችንንም ከወያኔ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት በምናደርገው ትግል የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪ አስተላለፈዋል። ይህን ታሪካዊ ጥሪ ለመመለስና የሀገርና የትውልድ ጠላት የሆነውን ወያኔ ሕወሃትን ለማስወገድ አብረን እንቁም ሕዝባዊ ሃይላችንንም ተቀላቀሉ ሲሉም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ምንጭ፣ ግንቦት 7

lørdag 10. mai 2014

የህውሃት/ወያኔ መሰሪ ስራ ለእኛ እንዳይተርፍ እንጠንቀቅ!!!

ከመሳይ በላይ !!!!
ህውሃት የሕዝቡን ሰምና መረጋጋት ለማግኘት፤ በሀገር ፀጥታና በብሔሮች ነፃ መውጣት ስም አምታትቶ፤ ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በመንፈግና የመሪዎችን ኪስ በማሳበጥ፤ የውሸት ሀገራዊ ዕድገትን ለመሸፋፈን መሞከሩ የትም አላደረሰውም። ይልቁንም በሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ቁማር መጫወቱ ራሱን ዞሮ መቶታል። መሠረታዊ የሆነውን የመንግሥት ተልዕኮ ስቷል።
በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መንግሥት ማለት፤ የሕዝብ ተወካይ ማለት ነው። መንግሥት ማለት በሕዝብ ፍላጎት የቆመ ማለት ነው። መንግሥት ማለት በሕዝቡ መካከል እኩልነትን የሚጠብቅና የሚያሰጠብቅ ማለት ነው። መንግሥት ማለት ለሕዝብ ደኅንነት፣ ለሰላምና ለሀገር ዕድገት የቆም ማለት ነው። መንግሥት ማለት የሕዝብ አገልጋይ ማለት ነው። ህውሃት ከላይ የዘረዘርኳቸውን አንዳቸውንም አላሟላም።
የደርግን መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝብ የጠላበት ምክንያት፤ በአረመኔነቱ፣ ያለሕግ የፈለገዉን በማድረጉ፣ የግለሰቡ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶች ባለመከበራቸው፣ በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ሠርቶ የማደርና የመበልፀግ በሩ በመዘጋቱ፣ የባለሥልጣኖች ወገን የሆኑ የሁሉም ነገር ፈላጭ ቆራጭ በመሆናቸው ነበር።
ታዲያ ህውሃት ግንባር መጥቶ የቀየረው ነገር ቢኖር፤ በደርግና በኢሠፓ ቦታ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መሪዎችና ፓርቲ መተካታቸውን ብቻ ነው። ግድያው፣እስራቱና የሀገር ሀብት ዝርፊያው ብሷል። ጥቂቶቹ በሃብት መጨማለቃቸውና አብዛኛው በድኅነት መማቀቁ የዕለት እውነታ ሆኗል። ህውሃት መሪዎችና ሀብት ነጣቂ አባሪዎቻቸው፤ የሕዝቡን የነፃነት ፍላጎትና ሠርቶ የማደር ጉጉት በስግብግብ የግል ጥቅም ማካበት ሩጫቸው አመድ አስጋጡት። ሀገሪቱን በጣጠቋት። ደንበሯን ሸጡት። ለሙን መሬት ከባለቤቱ ነጥቀው ለራሳቸውና ለውጭ ከበርቴዎች በርካሽ ቸበቸቡት። ይህ የሕዝቡን ቁጣ አስነስቶ መቃብራቸውን እንዲቆፍር ገፍቶታል። ለሥልጣናቸው በር መክፈቻ የተዋቀረው የክልል ግዛት፤ እንዳቋቋመው ፌዴራላዊ ግዛት ውስጡ በስብሶ ንቅዘቱ ሕዝቡን ቀስቅሶታል። ይህን ማስተካከል አሁን የሕዝቡ ኃላፊነት ነው። የአንድ ቡድን ወይንም ፓርቲ ግዴታና ውዴታ አይደለም። በአንድነት መስራት የሁላችን ነው። ህውሃት በሌላ አንድ ፓርቲ ባሁኡ ሰዓት ለመለወጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት አይደለም። ሀገር አቀፍ የሆነ አንድነትንና ሰላምን ማግኘት ነው የሕዝብ ፍላጎት። እኛ ከብዛታችን፣ ከሀብታችን፣ ከዕውቀታችን፣ ከሀገር ወዳድነታችንና ለወገናችን ካለን ፍቅር የተነሳ፤ የበለጠ ማድረግ የምንችል ነን። የጎደለን ነገር ቢኖር፤ በአንድነት የመሰባሰቡ ጉዳይ ነው። አንድ ስንሆን፤ አይደለም የትግሬዎችን ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ማስወገድ፤ ሀገራችን በብልፅግና ከዓለም ጎላ ብለው ከሚታዩት አንዷ መድረግ እንችላለን። የሚያሳዝነው ሀቅ ደግሞ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ብቻውን እስከቆመና እስከታገለ ድረስ፤ አቸነፈም አላቸነፈም ውጤቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሳይሆን የዚያ ድርጅት ብቻ ነው። መነሻው ባሁኑ ሰዓት ሕዝቡን እኔ ብቻ እወክላለሁ የሚል አንድ ድርጅት የለምና ነው። የተለያዩ የነፃ አውጪ ግንባሮች ኢትዮጵያዊ ያልሆነ አጀንዳቸውን እያራመዱ ነው። የውይይቱን ይዘት እነሱው አሽከርካሪ ሆነዋል። በተደራቢ ደግሞ፤ ሥልጣን የቋመጡ ግለሰብና ቡድኖች አራጋቢ በመሆን ይኼንኑ እየገፉ ነው። ይኼ የነገን አይቀሬ ጠብ አድልቦታል። መለየት ያለበት፤ ይህ የኢትዮጵያዊያን ትግል ነው ወይንስ የሌሎች የሚለው ነው። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እምነት ያለን ማንኛችንም ታጋዮች፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ወሳኝነቱን ተቀብለን ባንድ ለመታገል ፍርሃት ሊኖረን አይገባም። ድርጅት የመታገያ መሣሪያ እስከሆነ ድረስ፤ አሁን የምንሻው ኢትዮጵያዊ የሆነ አንድ ድርጅት ነው። ህውሃት(ሕዝቡ በትግሬዎች ነፃ አውጪ መንግሥት) የዕለት ተዕለት ፀረ-ኢትዮጵያ ተግባር ከቀን ወደ ቀን አንጀቱ እያረረ ነው። የመሪዎቹን ኪስ ማበጥ በዓይኑ እየተመለከተ ወገኖቹ በየመንገዱ እየተራቡ ማየቱ ዘግንኖታል። ሀገር እየተቆራረሰች ነው። በየክልሉ የተመደቡት ኩልኩል አገልጋዮች የክልላቸውን ሰዎች የግል ባሪያዎቻቸው እያደረጓቸው ነው። የውሸት ምርጫው ሕዝቡን እንደማያሳትፍ በተደጋጋሚ ታይቷል። የሚያጋልጡ ግለሰቦች ጥቃቱ በተደጋጋሚ ሕይወታቸው ማጣት ሆኗል። በትግሬዎቹ ነፃ አውጪ ግንባር ባለሀብቶችና በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል ያለው የኑሮ ልዩነት መለኪያ በሌለው ክፍተት ተራርቋል። ሥልጣንና ሀብት በተወሰኑት እጅ መካተቱ ትግሉን በጣም ለይቶ አውጥቶታል። በተደጋጋሚ ለገጠመው እድል በሩን ግጥም አድርጎ በመዝጋት፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ራሱን አግልሎ አስቀምጧል። ይህ ትግል፤ የጠራ ራዕይና አንድ ትክክለኛ ድርጅት እስካላበጀ ድረስ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድል በቀጠሮ ለወደፊቱ ተላለፈ ማለት ነው። እናም ደጋግመን ማንሰላሰል ያለብን፤ ጥረታችን የኢትዮጵያን ሕዝብ የትግል ግብ ገሀድ ለማድረግ እንጂ፤ ለመጪዎቹ ትግል ለማውረስ እንዳይሆን ነው። ሌባ ቀጪ አጥቶ ለሕዝብ አገልግሎት በሚውል ገንዘብ ደልቦ ሲንጎማለል ይውላል። ተጠቂው ሰፊው ሕዝብ አቧራ ለብሶ ለዕለት ጉርሱ ይማስናል። ፍትሕ የናፈቃት ዓለም። በየጥጋጥጉ ዲስኩር ብቻ ተለጥፎ ይነበባል!‹‹በመፈክር ውስጥ የተሸጎጡ በርካታ ውሸቶች አሉ፤›› “ነጻ ስለመሆን የማንንም ፈቃድ አንጠይቅም። ሰው በሰውነቱ የሚከበርበትአገር እስከምንመሰርት ድረስ እንታገላለን። የብሶታችንና የትግላችን መነሻለናንተ ለኔ አዲስ ትግል አይደለም” መብታችን ይከበር ነው የምንለው፣ ነፃነት ያስፈልገናል፣ማንም እንዳሻው ተነስቶ ህወሃትን አምልኩ እንዲለን አንፈቅድም! ግን ለምንድን ነው እርስ በእርስ እየተሻኮትን ለወያኔ እድሜ የምንጨምርለት? ፖለቲከኞቹሰ ብንሆን የምንታገለው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነው ካልን ልዩነታችንን አጥበን አንድ ላይ ማበር ያልቻነው ለምንድን ነው? ህዝቡ አንድ በሆነበት ሰዓት በፖለቲካው ድርጅቶች ርዕዮተዓለም መከፋፈል ምክንያት ህዝቡን ከጨቋኝ ስርዓት መታደግ ያልተቻለበት ግዜ ላይ መሆናችንን አስተውለናል ካላስተዋልን እናስተውል እንጂ! ዛሬ በዚህ ወሳኝ ትግል ምዕራፍ በሆንበት ወቅት ላይ ሆነን አንድነታችን ካልታየ ነገ ደግሞ እንደፈራነው ስንታገል የነበርነው ድርጅት እራስ በራሳችን መሻኮት ልንጀምር ነው ማለት ነው ኧረ ጠንቀቅ እንበል!!
ከመሳይ በላይ

የአበበ ገላው “ጩኸት” አንደምታ

የአበበ ገላው “ጩኸት” አንደምታ
May 10, 2014
ዳጉ ኢትዮጵያ (dagu4ethiopia@gmail.com)
አንድ የማህበራዊ ድረ-ገጽ ወዳጄ “በአበበ ገላው የሰሞኑ ድርጊት ምን አስደሰተህ?” ሲል ግራ በመጋባት ጠየቀኝ፡፡ የወዳጄ ጥያቄ የአበበ ገላው በፕሬዚደንት ኦባማ ፊት የኢትዮጵያውያንን የነፃነት ጩኸት ማስተጋባት በኔ በኢትዮጵያ ምድር የምኖር ዜጋ ላይ ስለሚኖረው አንደምታ በጥልቅ እንዳስብ አደረገኝ፡፡Abebe Gellaw confronting president Obama
ዜጎች ሐሳባቸውን በነጻነት መግለጽ በማይችሉባት ሐገር፤ ይልቁንም “ለዚህ ሥርዓት ጥሩ አመለካከት የለህም፣ የወጣት ሊግ፣ የሴቶች ፎረም፣ የነዋሪዎች ፎረም ወዘተ በተሰኙ የስርዓቱ አደረጃጀቶች አልተሳተፍክም” በሚል – መገለል፤ ባስ ሲልም መዋከብና ከስራ መፈናቀል በሚደርስበት ሐገር የማስበውን የሚተነፍስልኝ፣ አንደበት የሚሆንልኝ ሳገኝ ብደሰት፣ ባሞግሰው – ጀግና ብለው ምን ይገርማል? የህዝቡን ይሁንታ አግኝቼ ተመርጫለሁ፣ ኮንትራት ተሰጥቶኛል ወዘተ የሚል ማመካኛ እየደረደረ በምከፍለው ግብር የሚተዳደሩ የህዝብ ንብረት የሆኑ ሚዲያዎችን ወደራሱ የግል ንብረትነት አዛውሮ ጠዋት ማታ ሳልጠግብ – ጠግበሃል፣ በሥራ አጥነት እየተንከራተትኩ – ሥራ በሽ በሽ አድርጌልሃለሁ፣ የኑሮ ውድነቱ አጉብጦኝ – ኑሮህ ተሻሽሏል እያለ የራሱን ሹማምንት ምቾት የኔ እንደሆነ አድርጎ ለኔው የሚለፍፍ ስርዓት ባለበት ሐገር የነጻነት ጥማቴን የሚናገርልኝን አበበን ባወድሰው የሚያስገርመው ምኑ ነው?
በአምቦ፣ ሐሮማያ፣ አፋር፣ ምዕራብ ወለጋ፣ ተምቤን፣ ጎንደር ወዘተ በወንድም እሕቶቼ፣ በእናት አባቶቼ ላይ የሚደርሰውን አፈና፣ ግርፋት፣ ከመኖሪያ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ አላግባብ ከስራ ማባረር ወዘተ ሳወግዝ “የ… ከተማ ነዋሪዎች መንግስት የወሰደውን እርምጃ አደነቁ… ከግድያው የተረፉትም አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠየቁ” እየተባለ በስርአቱ የፕሮፖጋንዳ አንደበቶች ጩኸቴን ስቀማ – ያልኩት ቀርቶ ለመንግስት ጆሮ የሚጥመው በኔ ስም ሲነገር – አበበ ትክክለኛውን ጩኸቴን ሲጮህልኝ እልል ብል፣ ትክክለኛ ብሶቴን ለአደባባይ ሲያበቃልኝ አበጀህ ብለው ተሳሳትክ የሚለኝ ማነው?
በሐገር ውስጥ በመሆን ስርዓቱ ያሰፈነውን የፍርሐት ቆፈን ወግድ ብለው በብዕራቸው ብሶቴን የተነፈሱልኝን፣ ጩኸቴን የጮሁልኝን ተቃዋሚዎች፣ በጋዜጠኝነት ሙያቸው አገዛዙ ያመጣብኝን የመረጃ ረሐብ ሊያስታግሱልኝ የሞከሩ ጋዜጠኞችንና ጦማሪያንን ሰብስቦ በፈጠራ ክስ በእስር ሲያጉራቸው አሰፈንኩት ብሎ ያሰበውን የህዝብ ድምጽ እርጭታ በነጎድጓዳማ ድምፁ የሰበረልኝን – ስርዓቱ ለሚዘጋው እያንዳንዱ በር በአንጻሩ በትግል የሚከፈት ሌላ በር እንደሚኖር በተግባር ያረጋገጠልኝን አበበን አበጀህ የኔ አንደበት ብለው ወዴት ላይ ነው ጥፋቴ?
“የዋህ ነህ – የአበበ ገላው ድምጹን ማሰማት ስርዓቱን አያፈርሰውም፣ ኦባማ በስርዓቱ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል፣ በአደባባይ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን በደል እንዲያወግዝ አያደርገውም” ይሉኛል፡፡ እኔስ እሱን መች ጠበቅኩና? ለተበዳይ በደሉ መሰማቱ በራሱ የድሉ መጀመሪያ መሆኑን አታውቁም? ለታፈነ ሰው ጩኸቱ ለአደባባይ መብቃቱ፣ በደሉ ለጆሮ መድረሱ በራሱ ስኬት ነው፡፡ እንጂማ ጀርባዬ ላይ ሆኖ የሚያጎብጠኝን፣ እንደ እንስሳ ስለ ሆዴ እንጂ ስለ ነጻነቴ እንዳልጠይቅ የሚያስፈራራኝን፣ ስራ፣ የመኖሪያ ቤት ወዘተ በጥረቴ ሳይሆን ለስርዓቱ ባጎበደድኩት መጠን የማገኘው ድርጎ ያደረገብኝን ስርዓት ወግድልኝ ብሎ የማሽቀንጠሩ ኃላፊነት የኦባማ ሳይሆን የኔ መሆኑን መቼ አጣሁት? ገዢዎቼ የወንበር ስስት፣ የስልጣን ስጋት ስላለባቸው የአቤን ድርጊት ከወንበራቸው ከመነቅነቅ አንጻር ሊመዝኑት ይፈልጋሉ፡፡ የኔ መስፈሪያ ሌላ ነው፡፡ የማይወክለኝን ከወንበሩ የመነቅነቁ፣ ከምርጫ ኮሮጆ በመጣ የዜጎች ይሁንታ ሳይሆን ከሩስያ በመጣ የኤኬ 47 ጠመንጃ ጉልበት መንግስትነትን የያዘውን ስርአት የማንኮታኮቱ የቤት ሥራማ የኦባማ አስተዳደር ሳይሆን የኛ የኢትዮጵያውያን የመሆኑን ሐቅ መቼ ሳትኩት?
ደግሞስ እውነትን በሐይል ለስልጣን መናገር ያለውን ጉልበት መቼ አጣችሁት? ይኸው አበበ አይደል እንዴ በሐገር ውስጥ በጠመንጃና በእስር ቤት ሐይል፣ በውጪ ሐገር በብልጣ ብልጥነት ሸፋፍነው ይዘውት የነበሩትን የአምባገነንነት ማንነት በአለም አደባባይ እርቃኑን አስቀርቶ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ለክውታ (ምናልባትም ለህልፈት)፣ የስርአቱን ቲፎዞዎችም ለከፍተኛ ብስጭት የዳረገው? ትግሉ ፈርጀ ብዙ መሆኑን አትርሱ እንጂ፡፡ የቀድሞው መሪ ድምጻችን ይከበር ብለው ወረቀት ይዘው አደባባይ የወጡ ወንድሞቻችንን ግንባር በአልሞ ተኳሾቻቸው አስነድለው መቼ ዝም አሉ? “ባንክ ሊዘርፉ ሲሉ ተገደሉ” ብለው በወጣቶቹ ወላጆች ላይ የስነ ልቦና ጦርነት አልከፈቱም? ይህን ግፍ ያዩ ብዙዎች በኢትዮጵያ ሰማይ የእውነትና የፍትሕ ፀሐይ መቼም አትወጣም ብለው ተስፋ እንዲቆርጡ አልደረጉም? ስለዚህ የአበበ ድርጊትም አፋኞቻችንን – “እውነት ታፍና መቼም አትቀርም፤ ጠመንጃም የእውነትን ወሊድ ያዘገየው ይሆናል እንጂ እስከወዲያኛው አያስቀረውም” የሚለውን ሃቅ በአእምሯቸው እንዲያቃጭል ማድረጉ በራሱ ድል አይደለም? ይልቁንም ክስተቱ የተፈፀመው የስርአቱ ጥቅመኞች ቀድሞ በአካል፣ ሞተውም በ”ራዕይ” የሚመሯቸውን ግለሰብ ልደት ለማክበር ተፍ ተፍ ሲሉበት በነበረው ወቅት መሆኑ በስርአቱ ደጋፊዎች ላይ የፈጠረውን የስነ ልቦና ጉዳት እስኪ ወደ ማህበራዊ ድረ-ገፆች ጎራ በሉና ታዘቡ!
“አበበ አንድ ግለሰብ ነው… ጩኸቱም ምንም ለውጥ አያመጣም” ይላሉ፡፡ እንዴ… የነፃነት መንፈስ እኮ ሁሌም ሲጀመር በአንድ ወይም በጥቂት ሰዎች ነው፡፡ ደግነቱ ግን ቶሎ ይዛመታል፡፡ ውቂያኖስ ሳይገታው፣ ፖለቲካዊ ድንበሮች ሳያስቆሙት፣ የመረጃ አፈና ሳያግደው ወደሺዎች ከዚያም ወደ ሚሊዮኖች ይጋባል፡፡ ምርጫ 1997ን ማስታወስ ይቻላል፡፡ ጥቂቶች የነፃነት መንፈስን ከታሰረበት ፈተው ለቀቁት፡፡ በወራት ጊዜ ውስጥ ከገጠር እስከ ከተማ – ከድሐ ጎጆ እስከ ቤተ መንግስት ተቆጣጠረው፡፡ ዛሬም በአበበ ገላው የተለኮሰው የነጻነት ችቦ የነጻነት እጦት ብርድ ሆኖ ያንዘፈዘፈንን በሙቀቱ ሲያፍታታን፤ የአምባገነንነት ትኩሳት ጭንቅላታቸው ላይ የወጣውን ገዢዎቻችንን ነበልባል ሆኖ ሲፈጃቸው መመልከታችን አይቀሬ ነው፡፡
እናም … እናም… እናም… በወንድሜ አበበ ገላው ሥራ ደስ ተሰኝቻለሁ – ተነቃቅቻለሁ – ተስፋንም ሰንቄያለሁ፡፡ ነገ ይህ የነፃነት ስሜት በአእላፋት ላይ ተጋብቶ ገዢዎቻችንን በየሔዱበት ሲያስጨንቅ፣ አንገት ሲያስደፋ፣ ሲያብረከርክና ሲያፍረከርክ አሻግሬ እያየሁ…

fredag 9. mai 2014

ኦባማ ከትክክለኛው የ(ኢትዮጵያ)ታሪክ ምዕራፍ ጎን ተሰልፈዋልን? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ኦባማ ከትክክለኛው የ(ኢትዮጵያ)ታሪክ ምዕራፍ ጎን ተሰልፈዋልን? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)
May 8, 2014
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የታሪክ ሸፍጥ
ፕሬዚዳንት ኦባማ “በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ” መሰለፍ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦ ሰጥተው በመግለጽ እራስን በሚያወድስ መልኩ በተግባር ሳይሆን በንግግር ብቻ በማነብነብ እርሳቸው “በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ” ተሰልፈዋል ብለው የፈረጇቸው ሰዎች አቋማቸውን እንዲያስተካክሉ በነገር ሸንቁጠዋቸዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 በተደረገው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተቀናቃኛቸው ከነበሩት ከሚት ሮምኔይ ጋር ባደረጉት ክርክር ፕሬዚዳንት ኦባማ የእራሳቸውን ክብር ለመጠበቅ ሲሉ እንዲህ ብለው ነበር፣ “…ያሜ ሪካን መንግስትና ያሜሪካ ፕሬዝደንት በታሪክ ቀኝ ምዕራፍ ቆመዋል ብለው አስረዱ፡፡ “በብዙ አጋጣሚዎች ፕሬዚዳንት ኦባማ “በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ” ላይ መሰለፍ የሞራል ልዕልናን የሚጠይቅ እንደሆነ በተደጋጋሚ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን በተለዬ መልኩ አሜሪካ በሰብአዊ መብት ጥበቃ መስክ ላይ ትኩረት ከማድረግ አንጻር ብቸኛዋ ልዕለ ኃያል እንደሆነች ተናግረዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2009 የኢራን ተቃዋሚዎች ወደ መንገዶች ሰልፍ ለማድረግ በወጡበት ጊዜ ኦባማ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ለፍትህ በጽናት የቆሙ ሁሉ በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ የተሰለፉ ናቸው፡፡“ የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ ጥቂት ዓመታት በኋላ ኦባማ ባደረጉት ንግግር እንዲህ የሚል ጥያቄ አቅርበው ነበር፣ “ማንኛችሁ ናችሁ በዚህ የስብሰባ አዳራሽ የተገኛችሁ ተሳታፊዎች መጭው ጊዜ ህዝቡን ነጻ ከሚያወጡት ይልቅ ሀሳብን ወይም ለውጥን የሚያፍኑ ይሆናል ብላችሁ የምትከራከሩ? ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በየትኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንደምትሆን አውቃለሁ፡፡“ በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ነውን?!Obamas failed Africa policy
ፕሬዚዳንት ኦባማ በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ባልተሰለፉት ላይ ጩኸታቸውን አሰምተዋል፡፡ ቭላድሚር ፑቲን ክሪሚያን በመውረር እና የሶሪያን አምባገነን መሪ የሆኑትን ባሽር አላሳድን እየደገፉ ስለሆነ “በተሳሳተ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ናቸው”፡፡ አላሳድ በእራሳቸው ህዝቦች ላይ አሰቃቂ የሆነ ግፍ እየፈጸሙ ስለሆነ በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ናቸው፡፡ በመካከለኛው ምስራቅ የአረብ አገሮች የሚገኙ ሁሉም አምባገነኖች ፕሬዚዳንት ኦባማ ወደ ትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንዲሰለፉ እስከሚነግሯቸው ድረስ ለአጭር ጊዜም ቢሆን በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ነበሩ፡፡ “ዩናይትድ ስቴትስ ከቀጥታው እና ከጠባቡ ትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ያላትን አቋም በፍጹም አታለሳልስም፡፡ “በአሁኑ ጊዜ በሁሉም የመካከለኛው የአረብ አገሮች ላይ ያለን አቋም በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ መሆናችንን ያመላክታል ምክንያቱም ንጹሀንን በአሰቃቂ እልቂት ከመታረድ እየጠበቅናቸው እና ለሁሉም ህዝቦች ሰብአዊ መብቶቻቸው እንዲጠበቁላቸው እምነት ይዘን አቋማችንን እያራመድን ስለሆነ ነው፡፡“ በማለት ፕሬዚዳንት ኦባማ ንግግር አድርገዋል፡፡ ተቃዋሚዎች ቀስ እያሉ በአረብ ከተሞች ወደ መንገዶች ለአመጽ በወጡ ጊዜ በብርሀን ፍጥነት ተገልብጠው የአረብ አገር አምባገነኖችን በመቀላቀል በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ እረድፍ ላይ ሰልፋቸውን አስተካክለዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት ኦባማ ባለው ዓመት በግብጽ የተካሄደውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ እርዳታ ላይ የዓመቱን ግማሽ እርዳታ በመልቀቅ “በዓለም ላይ በጣም ጠንካራ የሆኑ ተዋጊ ሄሊኮፕተሮችን“ በትዕዛዝ ማስተላለፍ እንዲቆም በከፊል ማዕቀብ ጣሉ፡፡ የኦባማ አስተዳደር ከግብጽ ጋር እንደ ቀድሞው ሁኔታ መሞዳሞዱን በቀጠለበት ጊዜ የግብጽ ወታደራዊ ጦር የሙስሊም ወንድማማቾችን ይደግፋሉ ብሎ የወነጀላቸውን 683 ዜጎች በይስሙላው ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት እንዲበየንባቸው አድርጓል፡፡ ከዚህ አንጻር ሲገመገም በእርግጥ ኦባማ በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ነው ወይስ ደግሞ በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ ላይ ነው የተሰለፉት?!
“ስለታሪክ” ማስመሰያነት እየተነገረ ያለው የተገላቢጦሽ ሁኔታ የሚያስገርም ነገር ነው፡፡ ማርክስ በማኒፌስቷቸው ላይ እንዲህ ብለው ነበር፣ “እስከ አሁን ድረስ ያለው የህብረተሰብ ትግል የመደብ ትግል ነው፡፡“ ሄግል የታሪክ ሂደት በፍጹም ሊገለበጥ አይችልለም ብለው ነበር፡፡ ማህተመ ጋንዲ በዚህ ጉዳይ ላይ የማይስማሙ መሆናቸውን በመግለጽ እንዲህ ብለው ነበር፣ “በጣም ውሱን የሆኑ ጽናት ያላቸው ያልተገደቡ መንፈሶች እና እምነቶች የታሪክን ሂደት ሊቀይሩ ይችላሉ፡፡“ ዱራንት “ከታሪክ ስህተቶች ትምህርት የማንቀስም ከሆነ እነርሱን ባሉበት ሁኔታ እንደግማቸዋለን“ ብለው ነበር፡፡ ናፖሊዮን “ታሪክ ምንም ነገር ሳይሆን ሰዎች በመግባባት የፈጠሩት አፈ ታሪክ ነው“ ብለው ነበር፡፡ ያም ሆነ ይህ ናፖሊዮን እና ከእርሳቸው በኋላ የመጡት ሌሎች ሁሉም አምባገነኖች ተጠራርገው በታሪክ የቆሻሻ ማስቀመጫ ውስጥ ለዘላለም ይኖራሉ፡፡
ኦባማ እና ኬሪ የአፍሪካን አምባገነኖች ተሸክመዋል፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ በትክክለኛው ወይስ በተሳሳተው የታሪከ ምዕራፍ ላይ ነው ተሰልፈው ያሉት?
እ.ኤ.አ በ2009 ፕሬዚዳንት ኦባማ በጋና አክራን ሲገበኙ ያሉት ታሪክ በጀግኖች አፍሪካውያን ላይ የሚኖር ነው፡፡ ለጀግና አፍሪካውያን/ት ያስተላለፉት መልዕክት የሚያበረታታ፣ በብሩህ ተስፋ የሚያስሞላ እና ጠንካራ ስሜትን የሚፈጥር ነበር… መሪዎቻችሁን ተጠያቂ እንዲሆኑ እና ህዝቡን ለማገልገል የሚያስችሉ ተቋማትን ለማቋቋም ስልጣን አላችሁ፡፡ በሽታን ልታሸንፉ ትችላላችሁ፣ የእርስ በእርስ ግጭቶችን ማቆም ትችላላችሁ፣ እናም ለውጥን ከታች ጀምሮ ማምጣት ትችላላችሁ፡፡ ይህንን ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ አዎ ትችላላችሁ፡፡ ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ ታሪክ በእንቅስቃሴ ላይ ነው፡፡ ኦባማ ቦቅቧቃዎቹን የአፍሪካ መሪዎች በአጽንኦ እስጠንቅቀዋቸዋል፡፡ “…ምንም ዓይነት ስህተት እንዳትሰሩ፣ ታሪክ በእነዚህ ጀገኖች አፍሪካውያን/ት ጎን ናት እናም መፈንቅለ መንግስት በሚያደርጉ ወይም በስልጣን ላይ እንደ መዥገር ተጣብቀው ለመቆየት ሲሉ ህገመንግስትን በሚያሻሽሉ አምባገነኖች ጎን አይደለችም፡፡ አፍሪካ ጠንካራ ግልሰቦችን አትፈልግም፣ የምትፈልገው ጠንካራ ተቋማትን ነው…የዜጎቻቸወን ፍላጎት የሚያከብሩ መንግስታት የበለጸጉ የበለጠ የተረጋጉ እና የበለጠ ስኬታማ ናቸው…“
እ.ኤ.አ ጁን 2013 “የአፍሪካን አምባገነኖች መንከባከብ“ በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚህ ትችት ላይ የአሜሪካ “ዲፕሎአገዛዝ” እና “ዲፕሎቀውስ” (በእራሴ አባባል የአሜሪካንን መንታ ምላስ የሰብአዊ መብት አስመሳይ ዲፕሎማቶችን አመለካከቶች፣ ድርጊቶች እና ባህሪያት ለመግለጽ የተጠቀምኩበት) ነበር፡፡ በዚያ ትችቴ ላይ የአሜሪካው የመንግስት መምሪያ ጸሐፊ ኬሪ በጸሐፊነት ዘመናቸው ብዙም የማይጠቅሙ እና በደንብ ጎልተው የማይታዩ የሰብአዊ መበት አጠባበቅ በኢትዮጵያ እንዲሁም በመላው አፍሪካ የሚያራምዱ መሆናቸውን ለመተንበይ ሞክሬ ነበር፡፡ “የኬሪ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በአፍሪካ የሰብአዊ መብት ፖሊሲ“ ላይ በአስመሳይነት በባዶ ቃላት ታጅቦ የሚሽከረከር ምናባዊ እንጂ “ትርጉም ያለው የሰብአዊ መብት ፖሊሲ ሽግግር በኢትዮጵያ በማድረግ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡“ በኬሪ የዉጭ ጉዳይ አስተዳደር ዘመን ቀደም ሲል ከነበሩት ከሂላሪ ክሊንተን በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ የተለየ ፖሊሲ እንደማያራምዱ እና ተመሳሳይ እንደሚሆን ለፖለቲካ መድረክ ትወና ምቹነት እና “በሽብርተኝነት ላይ ዓለም አቀፍ ጦርነት” ለማካሄድ በሚል ማካካሻ የተረሳ እንደሆነ ትንበያ ሰጥች ነበር፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ህልውናቸው በአምባገነኑ ገዥ አካል ሲሸበብ፣ በጠራራ ጸሐይ የህዝብ ድምጽ ሲዘረፍ፣ ሰላማዊ አመጸኞች መብቶቻቸው ሲደፈጠጡ፣ እና የተቃዋሚ ኃይሎች ሀሳቦቻቸውን እንዳይገልጹ ሲታፈኑ፣ የፕሬስ እና የኢንተርኔት ገደብ ሲጣል እንዲሁም ሙስና በኢትዮጵያ እንደ ካሰንሰር እየተስፋፋ የአገሪቱን ሀብት እያሽመደመደ ባለበት ሁኔታ የኦባማ አስተዳደር ለሁኔታዎች አይቶ እንዳላየ እያለፈ ነው፣ ለጉዳዩም ምንም ትኩረት ባለመስጠት ጆሮ ዳባ ልበስ ብሏል፣ ከንፈር ከመምጠጥ ያለፈ ተጨባጭነት ያለው ስራም አልሰራም፡፡ ቃል እና ተግባር ለየቅል ሆነዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የኦባማ የአፍሪካ ፖሊሲ የሰብአዊ መብት ጥበቃን አያካትትም፡፡
ኬሪ ባለፈው ሰኔ ኢትዮጵያን በጎበኙበት ጊዜ በሰቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ላይ እየተደረገ ያለውን የኃይል እርምጃ እዲቆም፣ ሁሉም የፖለቲካ አስረኞች እንዲፈቱ እንዲሁም ነጻውን የመገናኛ ብዙሀን መጨቆኑን እንዲያቆም፣ ነጻ ጋዜጠኞችን፣ ሰላማዊ አመጸኞችን እና የተቃዋሚ ፖለቲካ አመራሮችን ማሸማቀቁን እና ወደ እስር ቤት ማጋዙን እንዲያቆም ይማጸ ናሉ ወይም ደግሞ እንዲያቆም ያደደርጋሉ የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ ይህንን ትንበያ በዘፈቀደ ወይም ደግሞ ከእውነታው በራቃ መልኩ ተምኔታዊ የሆነ አስተሳሰብም አልነበረም፡፡ ኬሪን እና ኦባማን በተናገሩት ቃላት ብቻ ነው እየመዘንኳቸው ያለሁት፡፡ እ.ኤ.አ በ2008 ዕጩ ተመራጮች የነበሩት ኦባማ እና ጆይ ቢደን የሚከተለውን ቃል ገብተው ነበር፣ “የታሰሩ ምሁራን፣ አክቲቪስቶች እና በግብጽ እንደ አይማን ኑር ያሉት የፖለቲካ የተቃዋሚ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ እንሰራለን፡፡” እ.ኤ.አ ጃንዋሪ 24/2013 በድምጽ ማሰባሰብ ሂደታቸው ላይ ኬሪ እንዲህ ብለው ነበር፣ “አንድ ወይም ሌላ አገር በምጎበኝበት ጊዜ ያለንን ቀዳሚ ዓላማ እና ይህም ተግባራዊ እንዲሆን በሚሉት ላይ አንዳንድ ጊዜ እጋፈጥ ነበር፣ ሆኖም ግን የሰብአዊ መብትን ጉዳይ በተለይም በእስር ቤት የሚገኙ ግለሰቦች እንዲለቀቁ ያላነሳሁበት ጊዜ አልነበረም፣ ይህንንም አቋሜን አጠናክሬ እቀጥልበታለሁ…“
ሴክሬታሪ ኬሪ እ.ኤ.አ በጁን 2013 ኢትዮጵያን በጎበኙበት ጊዜ በዲፕሎማክራሲያዊነት ጸጥ የማለት መብታቸውን ተጠቅመዋል፡፡ ኬሪ ለአምባገነኖቹ ስለሰብአዊ መብት ጥበቃ አንዲትም ቃል ትንፍሽ አላሉም፡፡ “የታሰሩ ምሁራን፣ አክቲቪስቶች እና የተቃዋሚ የፖለቲካ እስረኞች ማለትም እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታዬ፣ አንዷለም አራጌ፣ ኦልበና ሌሊሳ፣ በቀለ ገርባ፣ አቡባከር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል፣ ካሚል ሸምሱ እና ሌሎችም በርካቶች እንዲፈቱ እንሰራለን፡፡” የሚለው ይቅር እና ስለሰብአዊ መብት ጥበቃ አንዲትም ቃል ትንፍሽ አላሉም፡፡
በኦባማ አስተዳደር የሰብአዊ መብት ዲፕሎክራሲ ይዞታ፣
ኬሪ ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን በጎበኙበት ጊዜ የእርሳቸው አስተናጋጆች አሸርጋጅ የገዥው አካል አዲስ በቁጥጥር ስር ያዋሏቸውን እና ወደ እስር ቤት የወረወሯቸውን የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን እና አባላትን፣ ነጻ ጋዜጠኞችን እና ጦማሪስቶችን እንዲሁም የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን በጥይት እየቆሉ የመቀበያ ስጦታ አድርገው ሰላምታ አቅርበውላቸዋል፡፡ ይኸ በእውነቱ ታላቅ ዘለፋ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉት ወሮበሎች በኦባማ የማስመሰያ አስተዳደር ላይ ምን ያህል መተማመን እንዳለባቸው የሚያመላክተው ተጫባጭ የግድያ እና የዘፈቀደ የእስራት ወንጀለኝነት መረጃ በመያዝ ኬሪ ከአውሮፕላን ሲወርዱ አቅርበውላቸዋል፡፡ “እህስ ኬሪ እንግዲህ ምን ይፈጠር!?“
ኬሪ “የደህንነት ጉዳዮችን” ለመወያየት ኢትዮጵያ ውስጥ ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን በዘፈቀደ እየተጋዙ በእስር ቤት ስለሚማቅቁት እና የዘፈቀደ ግድያ ስለሚፈጸምባቸው የኢትዮጵያ ዜጎች ደህንነት ጉዳይ እልነበረም፡፡ ኬሪ ከእራሳቸው ፍላጎት ውጭ በተጽዕኖ ባለፈው ሳምንት በሸፍጥ ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ቤት የሚገኙትን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮቸን እና ደጋፊዎችን በማስመልከት የይስሙላ ንግግር አድርገዋል፡፡ የእስር ቤቱ ሰለባ ከሆኑት ከብዙዎቹ ጥቂቶች መርከቡ ኃይሌ፣ ሶሎሞን ፈጠነ፣ ዘሪሁን ተስፋዬ፣ አናኒያ ኢሳያስ፣ ፋሲካ ቦንገር፣ ጀሚል ሽኩር፣ ሰይፈ ጸጋየ፣ የሽዋስ አሰፋ፣ እመቤት ግርማ፣ ዮናስ ከድር፣ እየሩሳሌም ተስፋው፣ አበራ ኃይለማርያም፣ አበበ መከተ፣ ብሌን መስፍን፣ አስናቀ በቀለ፣ መስፍን፣ ተስፋዬ አሻግሬ፣ እዮብ ማሞ፣ ኩራባቸው፣ ተዋቸው ዳምጤ፣ ፍቅረማርያም አስማማው፣ እያስፔድ ተስፋዬ፣ ጋሻው መርሻ፣ ተስፋዬ መርኔ፣ ሀብታሜ ደመቀ፣ ጌታነህ ባልቻ፣ ንግስት ወንድይፍራው፣ ሜሮን አለማየሁ የሚባሉ ለሀገራቸው ብሩህ ራዕይ ያላቸው ወጣቶች ይገኙበታል፡፡
“ከውጭ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጋር በመገናኘት እና የማህበራዊ መገናኛዎች ዘዴዎችን በመጠቀም በአገሪቱ ውስጥ አለመረጋጋትን ለመፍጠር“ በሚል ሰበብ ገዥው አካል በሸፍጥ ያሰራቸውን ጋዜጠኞች እና ጦማሪስቶች እንዲፈታ ኬሪ የተማጽዕኖ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከእነዚህ ከታሰሩት ውስጥ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ አቤል ዋቤላ፣ አጥናፍ ብርሀኔ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት እና በፈቃዱ ኃይሉ ይገኙበታል፡፡
ስለአዲሶቹ ታሳሪዎች አዲስ ዜና ከአሜሪካ የመንግስት መምሪያ ምላሽ የሚጠበቅ ነበር፡፡ ኦህ እንዴት ያሰለቻል! የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት ጄን ሳኪ በዲፕሎክራሲያዊ መልኩ እንዲህ በማለት ገልጸው ነበር፣ “የኢትዮጵያ መንግስት ለእስር የዳረጋቸውን እስረኞች ጉዳይ እንደገና እዲመረምር እና በአስቸኳይ እንዲፈታቸው እንጠይቃለን፡፡ ይህንን ጥያቄ በቀጥታ ለኢትዮጵያ መንግስት ያቀረብነው በተጨባጭ በመሬት ላይ ያለውን እውነታ ከግንዛቤ በማስገባት ካለን አሳሳቢ ሁኔታ በመነሳት ነው፡፡ እናም በእርግጥ እኛ ከረዥም ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ ስለፕሬስ ነጻነት እና ሀሳብን በነጻ መግለጽ መከልከል ያለንን ስጋት በተደጋጋሚ በመግለጽ የኢትዮጵያ መንግስት የእራሱን ህገመንግስት ሙሉ በሙሉ እንዲያከብር ተማጽዕኖ ስናደርግ ቆይተናል፡፡“
እ.ኤ.አ ጁን 2012 የኢትዮጵያ ነጻ ጋዜጠኞች በይስሙላው ፍርድ ቤት ክስ በተመሰረተባቸው እና የረዥም ጊዜ እስራት በተፈረደባቸው ጊዜ ቃል አቀባይ ቪክቶሪያ ኑላንድ እንደዚሁ ተመሳሳይ ንግግር በማድረግ እንዲህ ብለው ነበር፣ “የኢትዮጵያ መንግስት በበርካታ ጋዜጠኞች እና በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ላይ የጸረ ሽብር አዋጁን በመጠቀም የመሰረተው ክስ አሳስቦናል…የነጻ ጋዜጠኞች መታሰር በመገናኛ ብዙሀን እና ሀሳብን በነጻ በመግለጽ መብት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ስላለው የሰብአዊ መብት አያያዝ ሁኔታ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የውይይት መድረክ በመክፈት ሀሳብን በነጻ የመግለጽ እና የመገናኛ ብዙሀን ነጻ ማድረግ የዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ ግንባታ ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን በማስመልከት ሀሳባችንን ግልጽ አድርገናል፡፡“ እንግዲህ እንደዚህ ባለ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ነው በኦማ አስተዳደር በተግባር እየተተረጎመ ያለው፡፡
ፕሬዚዳንት ኦባማ ከተሳሳተው የአሜሪካ ታሪክ ምዕራፍ የጎን ተሰልፈዋልን?
ኦባማ መጀመሪያ ፕሬዚደንት ሲሆኑ የስልጣን የመክፈቻ ንግግራቸው እንዲህ ብለው ነበር፣ “አሜሪካ በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ያሉ ባለስልጣኖች እውቀቱ ወይም ደግሞ ራዕይ ስላላቸው ብቻ አይደለም የምንተገብራቸው ሆኖም ግን የእኛ ህዝቦች የአያት ቅድመ አያቶቻችን መርሆዎች ታማኞች ሆነን ለመቀጠል ካለን ጽኑ ፍላጎት አንጻር ነው፡፡“ “ኦባማ ከአፍሪካ አምባገነኖነች ጎን በሚቆሙበት ጊዜ ከአያት ቅድመ አያቶቻችን መርሆች እና ከመመስረቻ ሰነዶች ተግባራዊ መሆን ጋር በጽናት ቆመዋልን?” የአሜሪካ ታላቁ የነጻነት አዋጅ የመመስረቻ ሰነድ የሚከተለውን ይላል፣
…መንግስታት ትክክለኛውን ስልጣን ከህዝቦች ፈቃድ በማግኘት የተዋቀሩ የሰዎች ስብስቦች ናቸው፡፡ የትኛውም ዓይነት መንግስት ለዓላማዎች ጎጅ ሆኖ ከተገኘ ይህንን መንግስት ለመለወጥ ወይም ደግሞ ለማስወገድ እና ደህንነታቸውን እና ደስታቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል በእነዚህ መርሆዎች ላይ በመመስረት የመንግስትን ኃይል ማዋቀር የሰዎች መብት ነው፡፡ ተከታታይ የሆኑ የመብት ረገጣዎች መፈጸም እና ከመብት ውጭ መሄድ እንዲሁም ባልተለያየ መልኩ አንድን ነገር በተግባር ማሳየት እራሳቸውን የለየላቸው አምባገነኖች በሚሆኑበት ጊዜ እንደዚህ ዓይነት መንግስታትን ከጫንቃቸው ላይ አሽቀንጥረው ለመጣል እና ለእነርሱ የሚስማሙ መንግስታትን ለወደፊቱ ደህንነታቸው ሲባል መመስረት የህዝቡ ስራ ነው…”
ኦባማ ስልጣንን ከጠብመንጃ አፈሙዝ በመያዝ ትክክለኛውን የህዝብ ይሁንታ ሳያገኙ በጉልበት ስልጣንን ጨብጠው ህዝብን በማሰቃየት ላይ ከሚገኙ የአፍሪካ ወሮበላ ገዥዎች እና አምባገነኖነች ጎን በሚቆሙበት ጊዜ ከነጻነት አዋጁ ጎን ቆመዋል ማለት ይቻላልን?
የአሜሪካን ነጻነት የሚያውጀው ታላቁ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ሰነድ የሚከተሉትን ኃላፊነቶች ይሰጣል፣
…ኃይማኖትን የማያከብር ወይም ደግሞ እምነትን ለማራማድ ክልከላ የሚጥል፣ በዚህም ሳቢያ ሀሳብን በነጻ የመግለጽ መብትን የሚሸብብ ወይም ደግሞ ነጻውን ፕሬስ የሚገድብ እና በነጻነት መሰብሰብን የሚከለክል እና ቅሬታን ለማቅረብ የሚከልክል መንግስት ህግ ሆኖ ሊወጣ አይችልም…ማንም ሰው ቢሆን ህይወትን፣ ነጻነትን ወይም ደግሞ ንብረትን ከህግ አግባብ ውጭ ሊያጠፋ ወይም ሊገድብ አይችልም፡፡
በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የእራሳቸውን ዜጎች ለሚፈጁ የአፍሪካ አምባገነኖች (ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል 47 የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን መግደሉን መዘገቡን ልብ ይሏል)፣ ነጻ ጋዜጠኞችን በእስር ቤት ለሚያማቅቁ የእምነት ነጻነትን ለሚያፍኑ፣ ዜፈጎች ሀሳባቸውን በመግለጻቸው ምክንያት የሚሰቃዩበት፣ በነጻ የሚሰበሰቡ ዜጎችንን የሚያስፈራሩበት እና የሚያሸማቅቁበት ያለምንም ተጠያቂነት ዜጎቻቸውን በሙስና ከሚዘርፉ ሌቦች ጎን ነው ኦባማ በትክክለኛ ምዕራፍ ተሰለፍኩ የሚሉት?
አብርሀም ሊንከን በጌቲስበርግ ንግግራቸው ላይ እንዲህ ብለው ነበር፣ “በእግዚአብሄር ፈቃድ ይህች አገር አዲስ የውልደት ነጻነትን የሚያጎናጽፍ የህዝብ መንግስት፣ ለህዝብ የቆመ ከመሬት አይጠፋም“ ብለው ነበር፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ ይህንን ሲሉ በአፍሪካ እጃቸው በደም ከተጨማለቀ ወሮበላ መንታፊ ገዥዎች ለመንታፊዎች ከተቋቋሙት “አዲስ የውልደት ነጻነት” ጎን መሰለፋቸውን ያመላክታልን?
የታሪክ ክስና ዳኝነት በኦባማ ላይ፣
ታሪክ ትክክለኛ የሆነ፣ ትክክለኛ ያልሆነ እና ውጣውረድ የሞላበት ከሆነ ታሪክም መክሰስም መዳኘትም ይቻላለል፡፡ የታሪክ ዳኝነት ሊሆን የሚችለው ኦባማ በትክክለኛው የታሪክ ምዕራፍ ላይ አልተሰለፉም፣ እናም ታሪክ እራሱ ከኦባማ ጎን አይደለም፡፡ ኦባማ ሁልጊዜ ከትክክለኛው የታሪክ ምዕርፍ ጎን እንደሚሰለፉ ይናገራሉ፣ ሆኖም ግን እውነታው ሲመዘን በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ ጎን ከተሰለፉት ጋር አብረው ተሰልፈው ይገኛሉ፡፡ ተግባር በተለይም የተሻለ ተግባር ከመናገር የበለጠ ይናገራል እናም በኦባማ ላይ የቀረበው ክስ በአፍሪካ ላይ በተሳሳተው የታሪክ ምዕራፍ ላይ በመሰለፋቸው የተመሰረተ ክስ ነው፡፡
በኦባማ ላይ የቀረበው ክስና ዳኝነት በአፍሪካ ከእርሳቸው በፊት ካገለገሉት ከጆርጅ ቡሽ ያነሱ ተግባራትን ነው ለአፍሪካ ያከናወኑት የሚል ነው፡፡ (ጆርጅ ቡሽን አልመርጣቸውም ወይም ደግሞ አልደግፋቸውም፡፡ ሆኖም ግን ስልጣን ለመስጠት ብቻ እውነታውን መናገር የለብኝም፡፡ በአሁኑ ጊዜ በስልጣን ላይ ሆነው ስልጣናቸውን እንዴት እየተጠቀሙበት እንዳሉ፣ የዜጎችን መብት በምን ዓይነት ሁኔታ እየደፈጠጡ እንዳሉ፣ ስልጣናቸውን ያለአግባብ እየተጠቀሙ እንዳሉ እና በአጭሩ ስልጣናቸውን ለበጎ ነገር መጠቀም ያለመቻላቸውን ያመላክታል፡፡) ቡሽ ገንዘባቸውን አፋቸው በተናገረው ቦታ ላይ ያስቀምጡ ነበር እናም በቢሊዮኖች የሚቀጠሩ ዶላሮች ኤች አይቪ ኤድስን ለመዋጋት እና በአፍሪካ የበሽታው ሰለባ የሆኑትን ወገኖች ለማገዝ ይጠቀሙበት ነበር፡፡ ኦባማ በግንባር ቀደምትነት ለዓለም አቀፍ የኤድስ ፕሮግም የሚውል በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ቅነሳ አድርገዋል፡፡ እንደ ዋሽንግተን ፖስት ዘገባ ከሆነ እ.ኤ.አ በ2012 በጠቅላላ 214 ሚሊዮን ዶላር ቅነሳ አድርገዋል፡፡ ይህም “በአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይህንን ቀሳፊ የሆነውን እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ በሬጋን አስተዳደር ጊዜ የተከሰተውን በሽታ ለማስወገድ አሜሪካ ተጨባጭነት ያለው ትግል ስታደርግ የቆየችበትን“ ኦባማ እ.ኤ.አ በ2014 ተጨማሪ 50 ሚሊዮን ዶላር ለመቀነስ ሀሳብ አቅርበው ነበር፡፡ የታሪክ ዳኝነት ሲመዘን ቡሽ በአፍሪካ የመጀመሪያ ገዳይ የነበረውን ወባን ከአፍሪካ ምድር ለማስወገድ አመርቂ የሆነ አስተዋኦ አድርገዋል፡፡ ቡሽ ለአፍሪካ ደኃ አገሮች የእዳ ቅነሳ አድርገዋል፡፡ ኦባማስ የፈየዱት ነገር ይኖር ይሆን?!? ካለስ እስቲ እንስማው፣ እንየው፡፡
ባለፈው ጁን ኦባማ አፍሪካን በጎበኙበት ጊዜ የጨለመውን የአፍሪካ አህጉር ለማብራት በሚል በርካታ የኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለማከናውን ተነሳሽነትን አሳይተዋል፡፡ “አፍሪካን በኃይል ለማጎልበት” በሚል መርህ ለሚቀጥሉት አምስት ተከታታይ ዓመታት በስራ ላይ የሚውል 7 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም ከዚሁ በተጨማሪ የግል ዘርፉን ለማጠናከር በሚል 9 ቢሊዮን ዶላር በተጨማሪነት ለመመደብ ቃል ገብተው ነበር፡፡ እስከ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ኦባማ ያጠናከሩት የወታደራዊ እና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ የአፍሪካን ወሮበላ ገዥዎች ኃይል ማጠናከር ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ቃል የተገባለቸው በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮች በባዶ ተስፋ በጆንያ ታጭቀው ለጨለማው አፍሪካ ወሮበላ አምባገነኖች የሚደርሱ ከሆነ ለመንታፊ የአፍሪካ አምባገነኖች በውጭ አገር ለከፈቷቸው የሂሳብ አካውንቶቻቸው እንደ ገና ዛፍ መብራት ከመስጠት ያለፈ ለብዙሀኑ የአፍሪካ ህዝብ የሚፈይዱት አንዳች ነገር አይኖርም፡፡
የታሪክ ዳኝነት ሲመዘን ኦባማ ለአፍሪካ ባዶ የተስፋ ቃላትን እና በማነብነብ ላይ ያነጣጠረ ባዶ ተስፋ ሆኖ ይገኛል፡፡ ላለፉት የመከኑ ቃል ኪዳኖች እንደገና ሌላ አዲስ ቃል ኪዳኖችን ይገባሉ፡፡ “በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን/ት ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በመምጣት በምርጥ ዩኒቨርስቲዎቻችን በመግባት እውቀታችሁን ማበልጸግ የሚያስችል አዲስ ፕሮግራም ተመቻችቷል“ የሚል አዲስ ቃል ኪዳን ገብተዋል፡፡ በአፍሪካ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን/ት በወሮበላ አምባገነኖች ስቃያቸውን የሚያዩት ወጣቶች የወደፊተ ዕጣ ፈንታ ሲተን ምን ምን ማድረግ ይቻላል?
የታሪክ ዳኝነት ሲመዘን ኦባማ በአፍሪካ የሚኖሩ ህዝቦች በእርሳቸው ቃል ኪዳን “ተስፋ እና ለውጥ” የወደፊት ጥሩምባ ጥሪ እምነት ጥለው የነበሩት ተስፋቸው ሲሟጠጥ ማየት አሳዛኝ ሁኔታ ነው፡፡ የኦባማ “የተስፋ መጠናከር” ምንም ያለማድረግ ተስፋ እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን/ት የባዶ ተስፈኛነት ምዕናባዊ ድርጊት ነው፡፡ የታሪክ ክሱ “ምንም የተደረገ ለውጥ እንደሌለ እናምናለን፡፡!“ በአፍሪካ ከወሮበላ አምባገነኖች እና ከእነርሱ ግብረበላ ሎሌዎቻቸው በስተቀር ማንም ቢሆን በኦባማ ላይ እምነት የለውም፡፡ የኦባማ “አዎ እንችላለን“ በተግባር ሲመነዘር “በአፍሪካ ውስጥ የሰብአዊ መብቶችን ሁኔታ ለማሻሻል ምንም ነገር ማድረግ አንችልም“ የሚል ግልባጭ ትርጉም ይዞ እናገኘዋለን፡፡
በአፍሪካ የተስፋ መጠናከር፣
ኦባማ እንዲመረጥ ሽንጤን ገትሬ ስታገል እና ሌሎችም ለኦባማ ደምጽ እንዲሰጡ ድጋፍ ሳሰባስብ ነበር፡፡ ይህንን ጉዳይ ግልጽ ላድርገው፡፡ ኦባማን በመደገፌ መቆርቆር ስሜት አይሰማኝም፡፡ አ..ኤ.አ በ2008 በተደረገው ምርጫ ኦባማ እንዲመረጡ ድጋፍ ባደረግሁ ጊዜ ያ ድርጊት ቆንጆ ሀሳብ ሆኖ ይታየኝ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ. በ2012 ምንም ምርጫ የሌለው ሆንኩ፡፡ ስለሚት ሮምነይ ምን ማለት እችላለሁ?! ጆን ሁንትስማን በሬፐብሊካን የምርጫ ዝርዝር ውስጥ አልነበረም፡፡ ምናልባትም እ.ኤ.አ በ2016 ሊሆን ይችላል፡፡
እ.ኤ.አ በ2008 ኦባማን ለመምረጥ የእኔ ውሳኔ የተመሰረተው ፍላጎታዊ እና የመጀመሪያው አፍሪካዊ አሜሪካ በመሆናቸው ብቻ አልነበረም፡፡ ኦባማ በህዝብ ላይ ያላቸውን አስተዋጽኦ ሪከርድ በማየት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ምርጫ ነበር፡፡ ከዩናይትድ ስቴትስ ሴኔት የህግ አገልግሎት ፋይላቸውን አጥንቻቸዋለሁ፣ እዲሁም ኦባማ HR 2003ን (ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እና ተጠያቂነት አዋጅ 2007) የሚያደንቁት እና ድጋፍም የሚያደርጉበት ስለነበር ነው፡፡ በኢሊኖይስ ህግ በደህንነት ፕሮግራሞች እና ዝቅተኝ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጎማ እንዲሰጣቸው እንዲሁም የቤተሰብ ሰራተኞች ከታክስ ነጻ እንዲደረጉ ሲያደርጉ የነበሩትን አስተዋጽኦ ከግንዛቤ በማስገባት ነበር ምርጫየን ያደረግሁት፡፡ በኢሊኖይስ ግዛት ሰራተኞች ከስራ እንዳይባረሩ እና ትላልቅ የምርት ተቋማትም እንዳይዘጉ ሲያደርጉት የነበረውን ጥረት አደንቃለሁ፡፡ እንዲሁም በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲያደርጓቸው የነበሩት መሳጭ እና ተያያዥ ንግግሮች እና በሚያቀርቧቸው በመረጃ ላይ በተመሰረቱ ጭብጦች እና የፖሊሲ መርሆዎች እገረም ነበር፡፡ “የአባታቸው ህልሞች” የሚለውን መጽሀፋቸውን በአንድ ቅምጥ በማንበብ፣ ሌሎችን መጣጥፎች እና ንግግሮቻቸውን በማዳመጥ እደሰት ነበር፡፡ በሀርቫርድ የህግ ትምህርት ቤት በነበራቸውን የአመራር ብቃት እና አካዳማያዊ ጥረት፣ በችካጎ የህግ ትምህርት ቤት በማስተማር ብቃታቸው ላይ ኩራት ይሰማኝ ነበር፡፡ እንደ መምህር እና የህገ መንግስት ባለሙያነቴ በሚያሳዩት አጋራዊ መንፈስ ኦባማ ጥሩ ብቃት ያላቸው ሰው አድርጌ እቆጥራቸው ነበር፡፡
ኦባማ የመጀመሪያው አፍሪካዊ አሜሪካ ፕሬዚዳንት መሆን በመቻላቸው ተጨማሪ እሴታቸው ነበር፣ ሆኖም ግን ይህ ለእኔ ወሳኙ ነገር አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ በ1968 ሮበርት ኬኔዲ ያደረጓቸው ነብያዊ ንግግሮች ለእኔ እና ለሌሎቸ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች አስገራሚዎች ነበሩ፡፡ እንዲህ ብለው ነበር፣ “እ.ኤ.አ በሜይ 1968 በሚቀጥሉት 40 ዓመታት ውስጥ እኔ የያዝኩትን ተመሳሳይ ስልጣን ጥቁር ሊይዘው ይችላል…“ “የኦባማ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጥ በዓለም ላይ በሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ሁሉ በተለይም በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ እና በአፍሪካውያን/ት “የተስፋን መጠናከር” በአሜሪካ በእራሷ በጉልህ እየታየ ስለሆነ የኦባማ ዕጩ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጥ ተቀባይነትን አግኝቷል– በአሜሪካ የማይቻለው የሚቻል ሆኖ ታይቷል፡፡ የኦባማ አባት ግንድ ከኬንያ መሆን በብዙ ሚሊዮን ለሚቆጠሩ አፍሪካውያን/ት ተስፋ የሰጠ ክስተት ስለነበር ኦባማ አፍሪካን በዩናያትድ ስቴትስ የውጭ ፖሊሲ ማውጣት እና በሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ጠንካራ ሚና በመጫወት የአፍሪካን ቦታ ከፍ ያደርጋሉ የሚል ግምትን አሳርፎ ነበር፡፡ በእነዚህ ምክንያቶች በኦባማ ላይ እምነት የመጣል የተስፋ ጥንካሬ ነበረኝ፡፡
የተስፋ ውሸት፣
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከኦባማ ያልተከበሩ ቃል ኪዳኖች እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን/ት ባዶ ተስፋዎች ምክንያት ከተስፋ ውሸቶች ጋር ግብግብ ገጥሜ እገኛለሁ፡፡ ሴናተር ኦባማ “የተስፋ መጠናከር“ በሚለው መጽሀፋቸው ላይ የአሜሪካንን የውጭ ፖሊሲ በሰብአዊ መበቶች ጥበቃ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመግለጽ ጆን ኬኔዲን በመጥቀስ እንዲህ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፣
በመንደሮች እና በጎጆዎች ያላችሁ በዓለም ላይ ግማሹን የምትይዙት የብዙሀኑን የመሰቃየት ማሰሪያ ገመድ ለመበጠስ የምትታገሉ ያለንን መልካም አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም የፈለገውን ያህል ጊዜ ቢወስድም እንኳ እራሳቸውን እንዲያግዙ ለማስቻል እንደግፋቸዋለን፣ ይህንን የምናደርገው ኮሚኒስቶች ስለሚያደርጉት ሳይሆን ወይም ድግሞ ድምጻቸውን ለማግኘት አይደለም፣ ሆኖም ግን ፍትሀዊ እና ትክክለኛ ስለሆነ ብቻ ነው፡፡ ነጻ የሆነ ህብረተሰብ ሌሎችን ደኃ የሆኑ ዜጎችን መርዳት ካልቻል ጥቂት ሀብታም የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችንም ማገዝ አይችልም፡፡
ለለውጥ አስፋለጊነት በሚያወሳው ንግግራቸው ሴናተር ኦባማ እንዲህ የሚል ጽሁፍ አቅርበው ነበር፣ “ባለፈው ምዕተ ዓመት በተደረገው ከእንግሊዞች አገዛዝ ነጻ ለመውጣት ጋንዲ ባደረጉት ዘመቻ፣ በፖላንድ የተደረገው የጋራ እንቅስቃሴ፣ ከጸረ አፓርታይድ ጋር በደቡብ አፍሪካ የተደረገው የነጻነት ዘመቻ ስኬታማ ስራ ምክንያት ዴሞክራሲ የአካባቢ መነቃቃት ውጤት ነው፡፡ ሌሎች ሰዎች የእራሳቸውን ነጻነት ለመቀዳጀት እንዲችሉ ማደፋፈር እና ልናግዛቸው ይገባል…መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው መብታቸው የተረገጡትን በአካባቢ አመራሮች ስም ልንናገርላቸው እንችላለን፣ የእራሳቸውን ህዝቦች መብት በተደጋጋሚ በሚደፈጥጡ አምባገነኖች ላይ የኢኮኖሚ እና የዴፕሎማሲ ጫና መጣል ይኖርብናል…“
“መብቶቻቸውን በተነጠቁ ዜጎቻችን ስም እንዲናገሩላቸው እና ነጻነታቸውን እንዲያስመልሱ“ ፕሬዚዳንት ኦባማ ለሚከተሉት ጀግና ኢትዮጵያውያን/ት ጥቂት ቃላትን ሊናገሩላቸው ይገባል፡ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ዉብሸት ታዬ፣ አንዷለም አራጌ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ በቀለ ገርባ፣ አቡባከር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል፣ መርከቡ ኃይሌ፣ ሶሎሞን ፈጠነ፣ ዘሪሁን ተስፋየ፣ አናንያ ኢሳያስ፣ ፋሲካ ቦንገር፣ ጀሚል ሽኩር፣ ሰይፈ ጸጋየ፣ የሽዋስ አሰፋ፣እመቤት ግርማ፣ ዮናስ ከድር፣ እየሩሳሌም ተስፋው፣ አበራ ኃይለማርያም፣ አበበ መከተ፣ ብሌን መስፍን… አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ አቤል ዋቤላ፣ አጥናፍ ብርሀኔ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት እና በፈቃዱ ኃይሉ…? ከዚህ የተስፋ ጥንካሬ ማህጸን ውስጥ የወጣ የውሸት ተስፋ ነው! “ኦ በመጀመሪያ ጊዜ ማታለል በጀመረንበት ጊዜ ምን ዓይነት የተወሳሰበ ድር እያደራን ነው”
የተስፋ እጥረት፣
ኦባማ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ላሉ አምባገነኖች እያዩ ያላዩ ያሉ በመምሰል እየተመለከቱ ነው፡፡ ለዓመታት ፕሬዚዳንት ኦባማ ለፕሬዚዳንት ሮናልድ ሬጋን ከበሬታን ሰጥተዋል፡፡ ምናልባትም ከሮናልድ ሬጋን ታሪክ መማር ይችላሉ፡፡ “እያንዳንዱ መንግስት የራሱ የሆነ ልዩ ባህሪ አሉት እናም ያ ባህሪ ከጠፋ መንግስቱም ይወድቃል፡፡ አምባገነናዊነት በተንሰራፋበት ስርዓት ፍርሀት አንዱ ነው፡፡ ህዝቡ አምባገነኑን መፍራት ባቆመ ጊዜ አምባገነኑ ስልጣኑን ያጣል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አገር ወካይ መንግስት በተዋቀረበት አገር ትልቅ ክብር እና ሞገስ ነው፡፡ ክብር እና ሞገስ በሌለበት ጊዜ መንግስቱ ይወድቃል፡፡ የፖለቲካ ጥርጣሬ እና የሞራል ጥያቄ ያለባቸውን መንገዶች እንመርጣለን? ክብር እና ሞገስን በመተው በእውነታ ላይ ብቻ እንኖራለን?… ይህ ከሆነ ከምናውቀው በላይ ለታሪክ ቆሻሻ መጣያ እየቀረብን ነው፡፡“ የታሪክ መጨረሻው በምጻት ቀን እና በሰው ልጅ ክብር እና ሞገስ መካከል ስልጣንን አላግባብ መጠቀም ሊሆን ይችላልን?
የታሪክ ዳኝነት ፕሬዚዳንት ኦባማ ለሚመጣው ትውልድ የአፍሪካ ዋና አባካኝ ተብለው የሚታወቁበት ይሆናል፡፡ እኛ አፍሪካውያን/ት በኦባማ ላይ ያለንን ተስፋ አቁመናል፡፡ ከባርነት በማምለጥ የነጻነት ሻምፒዮን የሁኑትን ታላቁን አሜሪካዊ የፍሬድሪክ ዳጉላስን ወርቃማ ቃላት በመዋስ፣ ”ማንኛውም ሰው በዝግታ ለምን ግድየለሽ እንደሚሆን እስቲ ተመልከቱ፣ እናም በእነርሱ ላይ የሚጫኑትን የኢፍትሀዊነትን እና ስህተትን ትክክለኛ መለኪያ ታያላችሁ፣ እናም ይህ ጉዳይ በቃላት፣ ወይም በኃይል ወይም በሁለቱም እስካልተወገደ ድረስ ድርጊቱ ይቀጥላል፡፡ የአምባገነኖቹ ወሰን በተጨቆኑት የዝምታ ጽናት ደረጃ ይገለጻል፡፡“
የኢትዮጵያ ህዝብ ጽናት ወሰኑ እስከምን ድረስ ነው? የአፍሪካ ህዝብስ?
ኦባማ ለኢትዮጵያ ደንታ አላቸውን? ለአፍሪካስ? ኦባማ ለማናቸውም ደንታቸው የላቸውም!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ሚያዝያ 28 ቀን 2006 ዓ.ም

mandag 5. mai 2014

የሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አሁንም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው

ሚያዚያ ፳፯ (ሃያ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ በሃሮማያ ዩኒቨርስቲ የተነሳው ግጭት አሁንም አስከፊ በሆነ መልኩ እንደቀጠለ ከአካካቢው የሚደርሱን መረጃዎች አመልክተዋል። የዩኒቨርስቲው ምክትል ዲን ዶ/ር ጨመዳ ችግሩ ከዩኒቨርስቲው አቅም በላይ መሆኑን ለተማሪዎች ተናግረዋል።

ባለፈው አርብ በተማሪዎች መካከል አካባቢን መሰረት አድርጎ በተነሳ ግጭት አንድ ተማሪ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደል አንዲት ሴት ተማሪም እንዲሁ ከፍተኛ የሚባል አካላዊ ጉድለት ደርሶባታል።
በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች መካነ ስላሴ ካቴደራል ተጠልለው ህዝቡ እርዳታ እያደረገላቸው ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ በግለሰቦች ቤት ተጠግተው ይገኛሉ። ከአለማያ ወደ ሃረር ተሳፍረው ለመጓዝ ሙከራ የሚያደርጉ ተማሪዎችም ተይዘው ይደበደባሉ።
በቅርቡ በዩኒቨርስቲው ውስጥ የፈነዳውን ፈንጅ እንዲሁም በተማሪዎች መካከል የተነሳውን ግጭት ተከትሎ ከ100 በላይ ቁስለኞች  በህይወት ፋና ሆስፒታል ተኝተው በመታከም ላይ ናቸው። ከእነዚህም መካከል ከፍተኛ ክትትል በሚደረግበት አይ ሲ ዩ በሚባለው ክፍል ውስጥ 7 ተማሪዎች መገኘታቸውም እንዲሁም፣ ሆዳቸው ፣ ጭንቅላታቸውና እግራቸው ውስጥ የቦንብ ፍንጣሪ ያለባቸው 8 ተማሪዎች በዚሁ ሆስፒታል እየታከሙ ይገኛሉ።
ለማ የሚባል የአባቱ ስም ያልታወቀ ተማሪም ሆስፒታል ከገባ በሁዋላ በማረፉ አስከሬኑን የሚወስድ ጠፍቶ በአስከሬን ማቆያ ውስጥ እንደሚገኝ የሆስፒታል ምንጮች ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ኦህዴድ በመካከለኛ ደረጃ ያሉ አመራሮችን ሰብስቦ ሰሞኑን በክልሉ ለታየው ግጭት የሌሎች ብሄር ተወላጆችን ተጠያቄ ማድረጉ ታውቋል።
በስብሰባው የተሳተፉ ምንጫችን እንደገለጹት ኦህዴድ የተማሪዎችን የመብት ጥያቄ የዘር ግጭት አስመስሎ ለማቅረብ መፈለጉ ፣ መንግስት ጉዳዩን ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እየወሰደው መሆኑን የሚያመለክት ነው። የአህዴድ ካድሬዎች ለተሰብሳቢዎች ” የአንድን ብሄር ስም እየጠሩ፣ ትናንት የገደሉን አንሶ አሁን ደግሞ ይሰድቡናል” በማለት መናገራቸውንና አንዳንድ ካድሬዎችም ይህንኑ በቁጭት ሲናገሩ እንደነበር ገልጸዋል።
ህወሃት በኦህዴድ አማካኝነት እየሄደበት ያለው መንገድ አደገኛ ነው የሚሉት ምንጫችን ፣ ህዝቡ በጊዜ ካልነቃ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ባወጣው መግለጫ በተማሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ፣ የደረሰውን የአካል ጉዳትና እስራት አውግዞ፣ አዲስ አበባ ማስተር ፕላንን ተግባራዊ ለማድረግ የሚደረገው እንቅስቃሴ እንዲቋረጥ እንዲሁም በተማሪዎች ላይ ግድያ የፈጸሙ ለፍርድ እንዲቀርቡ እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ ፖለቲከኞቸ ፣ ጋዜጠኞችና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ጠይቋል።

søndag 4. mai 2014

ኢትዮጵያ በህግ አምላክ የሚባልባት ሀገር መሆኗ ቀርቷል – ግንቦት ፯


May 3/2014

ግፈኛውና ዘራፊው የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያ መሬት ከሚሰራቸው ትልልቅ ወንጀሎች አንዱና ምናልባትም ዋነኛው በህግና ሕገ-መንግስት ላይ የሚያካሄደው ቀልድና ጭዋታ ነው። ሕገ-መንግስት ህዝብን ከእብሪተኛ መንግስት መጠበቂያ መሳሪያ መሆኑ ቀርቷል። ህግና ሕገ-መንግስት ለወያኔ ሲፋጅ በማንኪያ ሲበርድ በጣት የሚበላ ነገር ነው። ወያኔና አፋኝ ስርአቱ ህግ የሚጠቅሱት ለራሳቸው ይጠቅመናል ባሉበት ሰዓት ነው። ህግ ለነሱ ካልተመቻቸው ተቀዶ የሚጣል ቆሻሻ ወረቀት ነው።
በኢትዮጵያ ምድር ዋናው ሕገወጥ ተቋም ራሱ ላወጣው ሕግ የማይገዛው ወያኔ/ህወሃት ነው። ለዚህ ነው “ለሚመለከተው አካል ከማሳወቅ ውጪ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ፈቃድ አይጠየቅም” የሚለውን ራሱ ያወጣውን ህግ ጥሶ ሰሞኑን ተቃዋሚዎችን ቁም ስቅላቸውን የሚያሳያቸው። ለዚህም ነው ሃሳብን በጽሁፍና በቃል ለመግለጽ ቅድመ ምርመራ እና እገዳ አይኖርም ብሎ ጽፎ፣ አለም አቀፍ የሰበአዊ መብት ድንጋጌዎች እንዳሉ ተቀብያለሁ ብሎ የተናገሩና የጻፉ ሰዎችን የሚያሳድደውና በሽብርተኝነት የሚከሰው።
ኢትዮጵያ “በሕግ አምላክ” የሚባልባት ሀገር መሆኗ ቀርቷል። ወያኔ ይህን ለህግ ትልቅ ክብር ያለውን የህዝባችንን የዘመናት እምነት ድራሹን በማጥፋት ላይ ይገኛል። ፍትህ በወያኔ አፋኞች መዳፍ እጅ ወድቃለች።
በዚያ አስከፊ የደርግ መንግስት ስርአት እንኳን ዳኞችን “እንዲህ ብላችሁ ፍረዱ” የሚል ትእዛዝ አልነበረም።
ዛሬ በየፍርድ ቤቱ አለም እየታዘበ የሚከናወን አይን አውጣ አሰራር እና የህወሃት የንጹሃን ዜጎችን የፖለቲካ መቀጣጫ ቤት ሆኖ ተለምዶል። ፍትህ እና ፍርድ ቤት እንዲዋረድ ሆኗል። ፍትህና ዳኝነት ራሱ በህወሃት የታሰረበት ጊዜ ነው።
ባለፈው ሳምንት ወያኔ አፍሶ ማእከላዊ በማስገባት የሚያሰቃያቸው የዞን 9 የኢንተርኔት ፌስቡክ ተጠቃሚዎች በሀገሪቱ ህገ መንግስት ከተለመደው መሰረታዊ መብታቸው ውጪ ያደረጉት ቅንጣት ወንጀል የለም። ወያኔ በፈራ እና በደነገጠ ቁጥር ሺህ ህግ ይጥሳል፡፡ ወያኔ ደግሞ ጥላውን የሚፈራ ድንጉጥ ተቋም ነው።
የኢትዮጵያን ህዝብ እንደ ጠላት እንጂ እንደ አብሮ ኗሪ ዜጋ ማየቱን ከተዎ የሰነበተውም ለዚህ ነው።
ዛሬ ራሱ ወያኔም እኛም በሕግና በሕጋዊነት ላይ ያለን ተስፋ ተሟጧል። ስለዚህም ነው ምርጫችን ይህን ህገ ወጥ የወንበዴ መንግስት በትጥቅ አልባም ይሁን በታጠቀ ሁለገብ አመጽ ማስወገድ ብቻ ነው የምንለው።
ት 7 የወያኔን አያያዝ አይተን የሁሉአቀፍ የአመጹን መንገድ ተከትለናል። ፈልገን ሳይሆን ተገደን በወያኔ ምርጫ የተመረጠልንን።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ወያኔ የህግና የሰላም በሩን ሁሉ ዘግቶ የተወልህን እና ሊከለክልህ የማይችለው ምርጫ የራስህን የነጻነት ትግል የአመጽ ሃይል ብቻ ነው። በየአለህበት በእምቢተኝነት ተነሳ!! መብትህንና ክብርህን ከወያኔ መጠበቅ የዋህነት ነውና ተነስ ተቀላቀል! ራስህን ነጻ አውጣ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

German Radio report on UDJ's 4 May 2014 protest march in Addis Ababa

በማእነደሁልጊዜው ሁሉ ህገ መንግስታዊ መብቶቻችን መጠየቅ እንቀጥላለን ሰርና በመደብደብና በመግደል የአገር ችግር አይፈታም !!!!!

ክቡራን የዞን ዘጠኝ ነዋሪያን

ሳምንቱ በአራማጅነት ቆይታችን ከነበሩን ጊዜያት መካከል በጣም ከባድ ሆኖ አለፈ። የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጅ ጋዜጠኛ ጓደኞቻችን ከታሰሩ 7 ቀናትን አሳለፋ፡፡ በሳምንቱ ውስጥ ቤተሰብና የህግ ባለሞያ ሳያገኛቸው እሁድ ቀን ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከመስማት ውጪ አያያዛቸውንም ሆነ ያሉበትን የጤንነት ሁኔታ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ እስካሁንም ቤተሰብም ሆነ የህግ ባለሞያ እነዲያያቸው አልተፈቀደም፡፡ ይህ በግልጽ ህገ መንግስቱን የሚጥስ የምርመራ ሂደት በማእከላዊ ሲካሄድ አዲስ አይደለም፡፡ ከዚህ በፌት የነበሩ የፓለቲካ እስረኞችም በተመሳሳይ ሁኔታ የመታየት መብታቸው ከማእከላዊ ጀምሮ ተነፍጎ አሁንም ቤተብሰብም ሆነ ወዳጅ እነዳይጎበኛቸው የተደረጉ እንዳሉ ይታወቃል ፡። ዞን 9 ከመጀመሪያ ዘመቻዎች አንስቶም ህገመንገስቱ አንዲከበረ ስንጠይቅ መቆየታችን ይታወቃል፡። ይህ መሆኑ ሳያንስ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን ሲጠቀሙ የነበሩ (ሶስተኛው የዞን ዘጠኝ ዘመቻ) የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች እስር የአካል ጉዳትና ሞት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ይህ በመላው አገሪትዋ እየታየ ያለውን ተቃውሞ መንግስት ምላሽ እየሰጠ ያለበት መንገድ አሳሳቢ አስፈሪና አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ ሳምንቱንም በሰብአዊ መብቶች ረገድ በጣም የከፋ ያደርገዋል፡፡Zone 9 bloggers
መንግስት የዞንዘጠኝ አባላትንና ጋዜጠኞቸን ሰርተዋል ብሎ ያቀረበው ወንጀል በማህበረሰብ ሚዲያ በመጠቀም ህዝብን ለብጥብጥ ማነሳሳት ነው ሲል የመንግስት ቃል አቀባይ በበኩላቸው በጻፉት ሳይሆን በወንጀል በመሰማራታቸው ነው የታሰሩት ብለዋል፡፡ ወንጀሉ ፓሊስ እንዳቀረበው ደግሞ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥን የማንሳት ተግባር ከአገር ውጨ ከሚገኝ ራሱን ከሰብአዊ መብት ብሎ ከሚጠራ ተቋም ጋር ተባብረው ብጥብጥ ማስነሳት ነው ብሎታል ፡፡ ክሱ በአጭሩ ሁለት ነገሮችን ይይዛል፡፡ አንደኛው በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማስነሳት ሲሆን ሁለተኛው በሃሳብና በገንዘብ ከውጪ ድርጅቶች ጋር መተባበር ነው ፡፡
ማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ?
በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ ማንሳት የሚል ክስ ለማቅረብ በማህበረሰብ ሚዲያ ብጥብጥ የሚያስበሱ መልእክቶቸን ማስተላለፍ ያስፈልጋል፡፡ በዚህ ረገድ ማንኛውም የዞን 9 ነዋሪያን እነደሚመሰክሩት ህገ መንግስታዊ መብቶች እነዲከበሩ ከመጠየቅና መንግስትን የሚተቹ ጽሁፎችን ከማቅረብ ባለፈ አንድም የዞኑ ስራ ለብጥብጥ እና ለሁከት ምክንያት ለመሆን የሚበቃም አይደለም፡፡ ይህንነ ለመረዳት የዞኑን ዘመቻዋች እና ጽሁፎች ማየት ብቻውን የክሱን አስቂኝነት ለማስረዳት ይበቃል፡፡ እስከዛሬ በጻፍናቸው የመንገስት ትችቶች ካልሆነ በስተቀር ባነሳሳናቸው ብጥብጦች አንታወቅም ፡፡ ለዚያም ነው በጽሁፋቸው አይደለም የታሰሩት የሚለውን የመንግሰት ማስተባበያ አስቂኝ የሚያደርገው ፡። በጽሁፍ ካልሆነ በምንድነው የዞን 9 አባላትን እንድ ላይ እንደቡድነ ሰብስቦ መክሰስ የሚቻለው??
ከውጨ ድርጅት ጋር መተባበር
ዞን 9 ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ላለፉት ሁለት አመታት በነበረው ቆይታ የተለያዩ አጋርነቶችነ ከተለያዩ አካላት ጋር ፈጥሮአል፡። በዚህም በተለያየ ጊዜ እነደግለሰብም አንደቡድን ተወካይ በመሆን አባላቱ አገሪትዋ ውስጥ ያለውን የሰብአዊ መብጥ ጥሰት አያያዝ አስመልክቶ ለተለያዩ ቦታዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ ኢንተርኔት ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደርጋቸውን አስተዋእጾም አስመልክቶ በቡድንም በነጠላም በተለያዩ ቦታቸዎች ላይ በመገኘት ልምዳቸውን አካፍለዋል፡፡ ይህ መንግስት ሲፈልግ የሚፈቅድላቸው ሲፈልግ ወንጀል የሚያስመስለው ተግባር ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጲያዊ ህገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡ ዜጎች በመጓዛቸው ስራቸውን እና ልምዳቸውን በማካፈላቸው እነዲሁም ራሳቸውን ብቁ በማድረግ የሚሰሩትን የሰብአዊ መብት እነቅስቃሴ ለሌሎች መናገራቸውን ወንጀል ለማስመሰል የሚደረገውን ጥረት አሁንም ቢሆን እንደዞን 9 አጥብቀን እናወግዛለን፡፡ ከዚህ በፌትም እነደተናገርነው በህግ እስካልተከለከለ ድረስ ህጋዊ እንቅስቃሴዎቸን መንግስት ስላልወደዳቸውና ህገ ወጥ ስላስመሰላቸው የምናቆምበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ሁሉም የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆች በፓርላማ በህገ ወጥነት ከተፈረጁ ተቋማት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አልነበራቸውም የላቸውምም፡። ለዞን ዘጠኝ ስራም ምንም አይነት የፋይናንስ ድጋፍ አግኝተን አናውቅም፡፡ (በመሰረቱ የፋይናንስ ድጋፍ የማያስፈልገው የበጎ ፍቃደኝነት ስራ ነው የምንሰራው ) ከዚያ ውጪ ግን በፓርላማ ህገ ወጥ እስካልተባሉ ወይም ከልካይ ህግ እስካልመጣ ድረስ ከተለያዩ በተባበሩት መንግስታት እውቅና ካላቸው የመብት ተሟጋች ተቋማት ጋር ያለንን ግንኙነት ወንጀል ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት አንቀበለውም፡።
አንዳንድ አስቂኝ የመንግስት ወዳጆች በህቡህ ተደራጅተው የሚል ክስም ሲለጥፉብን ሰምተናል፡፡ ህቡህ ማለት ምን ማለት እነደሆነ ትርጉሙን እንዲያጣሩ ከመጠየቅ ባለፈ ምንም የምንጨምረው ነገር የለንም ፡፡ ባለፉት ሁላት አመታት ቆይታችን ፎቶአችን የሚታይ ሙሉ ህጋዊ ስማችን የሚታወቅ አገር ውስጥ የምንኖር ኢንተርኔት ላይ የተናገርነውን በግንባር የምንደግም ህጋዊ ዜጎች ነን፡። ከዞን ዘጠኝ እሴቶች መካከልም አንዱ ለተናገሩትም ሆነ ለሚያስተላልፉት መልእክት ሙሉ ሃላፌነትን መውሰድም ጭምር ነው ፡፡ በመሰረቱ ኢንተርኔት ላይ ቡድን መመስረት በየትኛውም ህግ የማይከለከል ህጋዊ ተግባር መሆኑን ለመንግስትና የመንግሰት እርምጃ ለደገፉ ለማስታወስ አንወዳለን፡፡
ባለፉት ቀናት ስንናገር እንደነበረው መንግሰት የዞን ዘጠኝ አባላትና ወዳጆችን እነዲፈቱ መጠየቁን አሁን ደግሞ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም በጋራ ድምጻችንን ማሰማታችንን እንቀጥላለን፡፡ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እየተደበደቡና እየሞቱ የዞን9 አባላትን እስር ብቻ ለይተን ዘመቻ ማድረጉን ሃላፌነት የሚሰማው ሆኖ አላገኘነውም፡፡ በመሆኑም ሁለቱ ጉዳዪች ላይ አተኩረን የሚመለከተው አካል ሃላፌነቱን እነዲወጣ ግፌት ለማድረግ እንሞክራለን፡። ዞን ዘጠኝ እንቅስቃሴን በማሰር ለመገደብ ቢሞክርም ብዙ የዞኑ ነዋሪያን ጋር በመተባበር ከምርጫ ጋር የተያያዙ ስራዎችን የመስራት እቅዳችነን አጠናክረን እንቀጥልበታለን፡።
ከነገ ሚያዝያ 25 ጀምሮ የዞን 9 ጦማርያንን እና ወዳጅ ጋዜጠኞችን መፈታት እነዲሁም በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የምን ቃወምበት መጠነ ሰፌ ዘመቻ እንጀምራለን፡፡ እስካሁን በተናጠል ላሳያችሁን ህብረት በከፍተኛ ሁኔታ እያመሰገንን በጋራ የአገራችንን “ዞን ዘጠኝተነት” በመቃወም ህብረታቸንን እናሳይ ፡።
የዘመቻውን ዝርዝር በሚቀጥሉት ፓስቶች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡