søndag 12. oktober 2014

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ በደህንነት ሰዎች ተደበደቡ

ፍኖተ ነፃነት
10710933_711118828973054_6184937440487717547_nየአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የሰሜን ቀጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ አዕምሮ አወቀ ሐሙስ ዕለት ከሥራ ወደ ቤታቸው ሲጓዙ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ እንደ አቶ አዕምሮ ገለፃ ይህ ድርጊት በየጊዜው እንደሚከሰትና በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት እንቅስቃሴ በደሴ ከተማ በመኪና ለማፈን በተደረገው ግብግብ መኪና ውስጥ አስገብተው እንደተደበደቡ ራሳቸውን ለመከላከል በሚታገሉበት ወቅትም ጋቢና የተቀመጠውን ሹፌር መኪናውን ለማስነሳት ቁልፍ እንደያዘ እጁን ሲረግጡት በመጎዳቱ፣ ሁለቱ ከኋላ የያዟቸውን ደህንነቶች ለመከላከል ባደረጉት ግብ ግብ ስላየሉባቸው ገፍትረው ከመኪናው እንደጣሉዋቸውና ወደ አዲስ አበባ ከመጡም በኋላ ወንድማችንን ደብድበሃል የትም አታመልጥም በሚል ለገሃር አካባቢ በቡድን ድብደባ እንደፈጸሙባቸው ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ከሰሜን የሚመጡ የፓርቲው አባሎችን ለመቀበል ዝግጅት በሚያደርጉበት ታህሳስ 17/2006 ዓ.ም ቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተሰብሮ ንብረቱ በሙሉ ከቤት ተጭኖ ተወስዷል፡፡ ሐሙስ ዕለትም ከሥራ ወጥተው በትራንስፖርት ወደ ቤታቸው በሚሄዱበት ወቅት አየር ጤና አካባቢ ከአውቶቡስ ሲወርዱ ሁለት ደህንነቶች ግራና ቀኝ እጃቸውን በመያዝ እንዳይንቀሳቀሱ ካደረጉዋቸው በኋላ ሦስተኛው ደህንነት በድንጋይ ከጉልበታቸው በታች ደጋግሞ በመምታት ቀኝ እግራቸው ላይ ጉዳት አድርሰው ሦስቱም ከአካባቢው እንደተሰወሩ ገልጸዋል፡፡ ይህ ህገ ወጥ ድርጊት በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌን እንዳቆም እንደማያደርገኝ ሊያውቁት ይገባል በማለት ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

søndag 28. september 2014

ስልጠና የሚያስፈልገው ላልሰለጠነው የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ነው!

ስልጠና የሚያስፈልገው ላልሰለጠነው የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ነው!

Sept 28, 2014

አምባገነኖች በውድም በግድም ህዝብ ስብሰባ ጠርተው ህዝቡ ፊት በቆሙ ቁጥር ሌት ከቀን የሚያባንናቸውን የተመረረ ህዝብ የነጻነት አመጽ የሚያስቀሩ ይመስላቸዋል። የህዝብ ሃብትና ጊዜ በከንቱ እንዳሻቸው እያባከኑ፣ ነጋ ጠባ ስብሰባ፣ ግምገማ፣ “ስልጠና” ወዘተ የሚጠሩት ህዝብ የነሱን ፍላጎትና ውሳኔ የኔ ነው ብሎ የሚቀበላቸው፣ የሚሰማቸው እና ፍርሃታቸውን ያቀለላቸው እየመሰላቸው ነው።
የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ሰሞኑን ተማሪዎችን፣ መምህራንን፣ ሰራተኞችንና መላውን ለፍቶ አዳሪ ተሰብሰብና እናሰልጥንህ የሚሉት በአገዛዛቸው የተንገፈገፈው ህዝብ ምሬቱ ወደ አመጽ እንዳይገነፍል ያደረጉ እየመሰላቸው ነው። ዲሞክራሲንና የህዝብ ወሳኝነትና ልእልናን በተቀበሉ ሀገሮች እንደወያኔና ቀደም ብሎ እንደነበረው የደርግ ስርአት የመንግስት ስብሰባ የማይዘወተረው ለዚህ ነው። የህዝቡን ፍርድ በስብሰባ እና በስልጠና እንደማያቆሙት ስለሚያውቁ ህዝብን ስለሚያከብሩ ነው።
ሰሞኑን በመላ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ወያኔዎች ‘ስልጠና’ ብለው የሚጠሩት፣ በይዘቱ አያቶቻችንን ድሮ ላውጫጪኝ ይጠቀሙበት የነበረውን አፈርሳታ የመሰለ የመደናቆሪያ ስብሰባ አላማው ግልጽ ነው።
አላማው ህዝብ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ ቢቻል ለማደንዘዝ ካልተቻለም ለማስፈራራት ነው። ግፍን፣ ፍትህ ጥፋትን ልማት፣ ጭካኔን፣ ርህራሄ ለማስመሰል አፈጮሌ ነኝ ያለ ካድሬ ሁሉ የምላስ ጂምናስቲክ የሚሰራበት ጉባኤ ነው። ከተሰብሳቢው ህዝብ ከረር ያለ ጥያቄ በመጣ ቁጥር መላ ቅጡ የሚጠፋቸውም ለዚህ ነው። እነሱ የተዘጋጁት የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ አይደለማ! የህዝቡን ጥያቄ እንደማይመልሱማ ያውቁታል።
ነገሩ መልከ ጥፉን በስም ይደገፉ ሆነና ይህንን ቧልት ‘ስልጠና’ ብለው ይጠሩታል። እነዚህ ራሳቸው መሰረታዊ ስልጣኔ የሌላቸው አሰልጣኞች መምህራኑን ስለትምህርት ጉዳይ ሊያሰለጥኗቸው ሲንጠራሩ አይፍሩም። ባለሙያውን ሁሉ በሙያው ካላ ሰለጠንህ ብለው ግዳጅ ስብሰባ ያጉሩታል። ይህ የወያኔ ተግባር እውቀትና ስልጣን ከተምታታባቸው የወያኔ ጉጅሌዎች ስለመጣ ብዙ ላያስገርም ይችል ይሆናል። እንደ ህዝብና እንደ ዜግነታችን ግን በያንዳንዳችን ላይ እየደረሰ ያለ ውርደት ነው። ወያኔ ካላዋረደንና ሰበአዊ ክብራችን ካላሳነሰ የሚገዛን አልመሰለውም።
ግንቦት 7 ውስጥ ያለን የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች ይህ ዘርፈ ብዙ ውርደት እንዲቆም ነው የምንታገለው። የኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ ዘመን ይህን በመሰለ ውርደት ውስጥ ሊኖር የሚገባው ህዝብ አይደለም ብለን እናምናለን። የማያቋርጠው ጥሪያችን ዛሬም ተመሳሳይ ነው። ፈልገናቸው ሳይሆን በሃይል ራሳቸውን የጫኑብንን የወያኔ ጉጅሌዎች ከጫንቃችን ላይ እናራግፋቸው።
በአንድነት እንነሳ! በያለንበት ለዚህ ውርደት እምቢ እንበል። ውርደታችን እምቢ ያልን ቀን ይቆማል። ያን እለት ጨለማው ይገፈፋል። የነጻነታችንና የክብራችን ጎህ ይቀዳል።
በያለንበት እምቢ እንበል! ስለተገፋንና ስለተዋረድን ማመፅ መብታችን ነው። የቻልክ ተቀላቀለን። ያልተመቸህ በያለህበት በራስህ አነሳሽነት ራስህን አደራጅ። የነጻነታችን ቀን ቅርብ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

lørdag 27. september 2014

የቅዳሜ ውሎ በቃሊቲ

 እስረኞች መብት አላቸው፡፡ አንዳንድ እስረኞች ግን ከሌሎቹ የተለየ መብት አላቸው፡፡ አንዳንዶቹ ምንም መብት የላቸውም››
ዛሬ ወደቃሊቲ አቅንተን ነበር፡፡ የእነ አቶ በቀለ ገርባ፣ የአዛውንቱ ሲሳይ ብርሌ፣ የጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ምክር፣ ትንታኔና ተስፋ አንዳች ጥንካሬ ይሰጣል፡፡ የእነዚህ ታሳዎች ጥንካሬ ቃሊቲ እስር ቤት መሆኑን ሁሉ ያስረሳል፡፡
political-prisoners-ethiopia2
መጀመሪያ እነ በቀለ ገርባን ጠይቀን ነው ወደ ጋዜጠኛው ያቀናነው፡፡ ውብሸትን ለመጠየቅ ስናቀና የገቢዎችና ጉምሩክ ምክትል የነበረው ገብረወሃድ እስረኞች ከሚጠየቁበት ውጭ አንድ ጥግ ላይ ከቤተሰቦቹ ጋር ሰብሰብ ብሎ አየነው፡፡ እስረኞች ወደሚጠየቁበት ስናመራ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዳይሬክተር የነበረው መላኩ ፋንታና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ለመጠየቂያነት የተከለለው ቦታ ላይ ጎን ለጎን ቆመው ከቤተሰቦቻቸው ጋር እያወሩ ደረስን፡፡
ከውብሸት ጋር ለተወሰኑ ደቂቃዎች ካወራን በኋላ ይበቃል ተባለ፡፡ ገና ወደ ውብሸት ስንመጣ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የነበሩት መላኩ ፋንታ አሁንም ከቤተሰቦቻቸው ጋር እያወሩ ነው፡፡ ገብረ ወሃድም እንደዛው፡፡ እንግዲህ በእስረኞች መካከል የሚፈቀደው የሰዓት ገደብም ይለያያል ማለት ነው፡፡ ለ‹‹አሸባሪ›› ጋዜጠኛ 10ና 20 ደቂቃ፣ ለ‹‹ኪራይ ሰብሳቢ›› ባለስልጣን ደግሞ የፈለገውን ያህል ጊዜ ይሰጣል፡፡
ያቆሰለኝ ግን ይህ አይደለም፡፡ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ከእናትና አባቷ ውጭ በማንም አትጠየቅም፡፡ እህቷ እስከዳርና እጮኛዋ ጋዜጠኛ ስለሽ ሀጎስ ርዕዮትን መጠየቅ ይቅርና ወደ ግቢው እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡ ውብሸትን ጠይቀን ስንወጣ ለመረዳት እንደቻልኩት እስረኞች ከሚጠየቁበት ውጭ አንድ ጥግ ይዞ ከቤተሰቦቹ ጋር ሰብሰብ ብሎ (ወንበርና ጠባብ ጠረጴዛ ነገር ቀርቦላቸዋል) በዓል እያከበረ የነበረውን ገብረወሃድ ብቻ አልነበረም፡፡ በእጮኛዋና በእህቷ እንዳትጠየቅ ከተደረገችው ርዕዮት ዓለሙ ጋር ታስራ የምትገኘው የገብረ ወሃድ ባለቤት ኮሎኔል ኃይማኖት ከባለቤቷና ከቤተሰቦቿ ጋር ሆና በዓል እንድታከብር ተፈቅዶላታል፡፡
የእኔ ጥያቄ ለምን እነ ገብረወሃድ ተፈቀደላቸው አይደለም፡፡ ነገር ግን ርዕዮት በእጮኛዋና በእህቷ እንዳትጠየቅ በተደረገችበት ወቅት እነ ገብረወሃድና ከርዕዮት ጋር ታስራ የምትገኘው ባለቤቱ ያለ ምንም የሰዓት ገደብ እንዲያውም እስረኞች ከሚጠየቁበት ክልል ውጭ በዓል እንዲያከብሩ መደረጉ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ‹‹እስረኞች መብት አላቸው፡፡ ነገር ግን አንዳንድ እስረኞች ከሌሎቹ የተለየ መብት አላቸው፡፡ አንዳንዶቹ ምንም መብት የላቸውም›› የሚል ያልተጻፈ ህግ እንዳለ ያሳያል፡፡ ህግ በእንሰሳዊ ስልት ለሌቦች አድልታ ስለ እውነት ለቆመችው፣ በብዕሯ ለህዝብ ለማሳወቅ ለጣረችው ወጣት ፊቷን ስታዞር አበቃላት፡፡ ይህ ርዕዮት ላይ ሆኗል፡፡ በቃሊቲ፣ በኢትዮጵያ ፍትህ እንዲህ አብቅቶላታል፡፡

fredag 26. september 2014

ጋዜጠኛ ውብሸት መንግስት ለተሰደዱ ጋዜጠኞች ዋስትና እሰጣለሁ ማለቱ ማታለያ መሆኑን ተናገረ

ነገረ ኢትዮጵያ
webshet tayeበሽብር ስም ጥፋተኛ ተብሎ በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ሰሞኑን መንግስት ከሀገር የተሰደዱ ጋዜጠኞች ወደሀገራቸው ቢመለሱ እንደማይከሳቸው በማስታወቅ፣ ለዚህም ዋስትና እሰጣለሁ ማለቱ ማታለያ መሆኑን በእስር ቤት ተገኝቶ ጋዜጠኛውን ለጎበኘው የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጠኛ ተናግሯል፡
አምስት መጽሔቶች እና አንድ ጋዜጣ መከሰሳቸውን ተከትሎ ሀገር ጥለው የተሰደዱ ጋዜጠኞች በሚሰሩበት ተቋማት ላይ የቀረበው ክስ የማይመለከታቸው በመሆኑ ወደሀገራቸው ተመልሰው በሙያቸው ሰርተው መኖር እንደሚችሉ፣ ለዚህም የኢትዮጵያ መንግስት ዋስትና እንደሚሰጥ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እውነቱ ብላታ ማስታወቃቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ‹‹ጋዜጠኞች አልተከሰሱም፤ ወደፊትም አይከሰሱምም›› ሲሉ ገልጸው ነበር፡፡
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ‹‹የመንግስትን ዋስትና መተማመን አይቻልም፤ የስርዓቱን ባህርይ ጠንቅቀን እናውቀዋለን፤ ዋስትና እሰጣለሁ ማለቱ ማታለያ ነው፡፡ በግሌ የሙያ አጋሮቼ ሀገር ቤት ሆነው የሚወዱትን ሙያ ቢሰሩ ደስ እሰኛለሁ፡፡ ሆኖም ግን ይህን መንግስት ማመን ከባድ ነው›› ብሏል፡፡
በተለያዩ እስር ቤቶች ታስረው የሚገኙ ጋዜጠኞችና ጦማርያን ለእስር የተዳረጉት ሀሳብን በነጻነት ከመግለጽ መብት ጋር በተያያዘ መሆኑን የሚያውቅ ያውቀዋል ያለው ጋዜጠኛ ውብሸት፣ የተሰደዱት ጋዜጠኞች ዋስትና አግኝተናል ብለው ቢመለሱ እንኳ የሙያ አጋሮቻቸው በእስር ለምን ይማቅቃሉ ብለው መጠየቅ እንደሚኖርባቸው አስተያየቱን ገልጹዋል፡፡
‹‹ኢህአዴግ የተሰደዱትን ዋስትና እሰጣለሁ ሲል አንድ ቁማር መጫወት ፈልጎ ነው፡፡ ይህም የተሰደዱትን አልከሰስሁም በማለት እናንተ ወንጀል አልሰራችሁም፤ በተለያዩ እስር ቤቶች ያሰርኳቸው ግን ወንጀል ስለፈጸሙ ነው የሚለውን ማስረገጥ በመፈለግ ነው፡፡ እኛ ወንጀል ሰርተን አይደለም የታሰርነው፡፡ ርዕዮት ዓለሙ ህክምና እንኳ እያገኘች አይደለም፡፡ ታዲያ መንግስት ዋስትና እሰጣለሁ ሲል ይህን ሁሉ ግፍ ይዘነጉታል ብሎ ነው እንዴ?›› ሲል ጠይቋል፡፡
እንዲሁ እንደ ቀላል ነገር ለተሰደዱ ጋዜጠኞች ዋስትና እሰጣለሁ ማለት ሌላ በተግባር እየተፈጸመ ያለውን ግፍ አይደብቅም ያለው ጋዜጠኛ ውብሸት፣ መንግስት ተራ ጨዋታውን ትቶ ወደልቦናው እንዲመለስ ጠይቋል፡፡ ‹‹ስርዓቱን 23 ዓመት አውቀነዋል፡፡ መታለል አይኖርብንም›› ብሏል ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ከቃሊቲ፡፡

onsdag 24. september 2014

በቂሊንጦ ግንቦት 7 ነው ተብሎ የታሰረው ወጣት 10 ጥፍሮቹን ነቅለው ብልቱ ላይ የላስቲክ ውሃ አንጠልጥለው እንዳሰቃዩት ተጋለጠ

(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 አባል ነው ተብሎ የታሰረው አበበ ካሴ የተባለ ወጣት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በሕወሓት/ኢሕአዴግ ካድሬ ወታደሮች ከፍተኛ የሆነ ግፍ እየተፈጸመበት መሆኑን ከስፍራው ለዘ-ሐበሻ መረጃ ያደረሱ ወገኖች አስታወቁ።
Breking News
“ዛሬ ከወደ ቂሊንጦ የደረሰኝ መረጃ እጅግ የሚዘገንና እንቅልፍ የሚነሳ ነው” በሚል መረጃውን ያቀበለን ውስጥ አዋቂ አበበ ካሴ ግንቦት 7 ነው በሚል የታሰረ ሲሆን መቀጣጫ እናደርግሃለን፤ ምስጢር አውጣ እያሉ በሚዘገንን መልኩ የ10 ጣቶቹን ጥፍሮች እንደነቃቀሉት አስታውቋል። እንደ መረጃ ምንጩ ገለጻ ከሆነ ብልቱ ላይ የታሸገ የላስቲክ ውሃ (ሃይላንድ) በማንጠልጠል ሲያሰቃዩት የቆዩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከብልቱ ፈሳሽ መውጣት መጀምሩም ተገልጿል። እንደመረጃ ምንጩ ገለጻ ከሆነ አበበ በብልቱ ላይ በደረሰበት ከፍተኛ ሕመም ህክምና እንዲደረግለት ቢጠይቅም “ሕክምና ማግኘት አይደለም ገና እንግድልሃለን” ብለው ከልክለውታል።
አበበ በአሁኑ ወቅት የእስረኛ መለያ መታወቂያውን መቀማቱን ያጋለጠው የመረጃ ምንጫችን የሚፈጸምበት ግፍ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ መምጣቱን እና እየተፈጸመበት ያለው የጭካኔ ተግባርም በምን ዓይነት ቋንቋ መግለጽ እንሚቻል ከባድ እንደሆነ ገልጾልናል።

søndag 14. september 2014

የቪኦኤ አማርኛ ሪፖርተር የሆነውና አወዛጋቢና የተዛባ መረጃ በማቅረብ በስፋት የሚታወቀው ሄኖክ ሰማእግዜር

በአበበ ገላው
የዛሬ ወር ገደማ የቪኦኤ አማርኛ ሪፖርተር የሆነውና አወዛጋቢና የተዛባ መረጃ በማቅረብ በስፋት የሚታወቀው ሄኖክ ሰማእግዜር ሙሉ በሙሉ ሃሰት የሆነ ዘገባ በአሜሪካን ሬድዎ አማካኝነት አሰራጨ። የዘገባው አላማ በካሊፎርኒያ የሚገኘው አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ ለአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሰጥቶ የነበረውን የክብር ሽልማት መልሶ መንጠቁንና ዝግጅቱ መሰረዙን በማስመልከት የቀረበው ዘገባ ሃሰት ነው ብሎ ለማስተባበል እና እኔን፣ አለማቀፉን የኢትዮጵያዊያን መብት የጋራ ህብረት እንዲሁም ኢሳትን በሃሰተኝነት ለመወንጀል የታለመ ነበር።Peter-Heinlein-Henok-Semaezer-Fente
ይሁንና ለእርምጃው ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ ያለው መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብት ጥሰት ዩኒቨርሲቲው እንዲመረምርና ሽልማቱን መልሶ እንዲያጤን ስለተደረገ መሆኑ በግልጽ የተነገረ እውነታ ነበር። ዩኒቨርሲቲውም ለክብሩ ስነ ስርአት መሰረዝ የሰጠው ዋነኛ ምክንያት ይሄው የሰብአዊ መብት ጥሰት ጉዳይ መሆኑን በይፋ ደጋግሞ ገልጿል።
አልተሳካም እንጂ ሄኖክ በተለይ በእኔ ላይ ያነጣጠረ በተንኮል የተሞላ ጎጂና የተዛባ ዘገባ ሲያቀርብ ይሄኛው ሶስተኛው ነው። በግንቦት 10, 2004 (May 18, 2012) በአቶ መለስ ዜናዊ ላይ የተቃውሞ ድሞጽ ሳሰማ ሄኖክ በአይኑ ያየው በጆሮው የሰማው ሃቅ ቢሆንም ድምጼን ሳንሱር አርጎ ዘገባውን አዛብቶ ለስርጭት አበቃው። በዚህም ምክንያት ቪኦኤ ከአድማጮቹ ከፍተኛ ተቃውሞ ስለቀረበበት በሳምንቱ ዘጋባውን እንደገና በሌላ ሰው አስተካክሎ ተቆርጦ የቀረውን ድምጼን አስገብቶ ሌላ ዘገባ ለማስተላለፍ ሞከረ። ይሄን በጋዜጠኝነት ስም የተሰራ እርካሽ የፖለቲካ ቁማር ታዝበን አለፍነው።
ከዛም ግኡሽ አበራ የሚባል አንድ የቦስተን ነዋሪ በእኔ ላይ የግድያ ወንጀል ለመፈጸም ሲዶልት ገና ከጥንስሱ በFBI ተደርሶበት ምርመራ እንደተደረገበት ተዘገበ። በዚህ ላይ ወያኔ የተቀናጀ ስራ በመስራት፣ አንዳንድ ድህረ ገጾችን፣ ፓልቶኮችን እና ቪኦኤን በመጠቀም እኔ ግኡሽ አበራን ልክ በሃሰት የወነጀልኩት ለማስመሰል ሌላ ያልተሳካ ጥረት ተደረገ። እንደተለመደው ሄኖክ አሳፋሪ የካድሬ ስራውን በመቀጠል ከፍተኛ መዛባት ለመፍጠር ሞከረ። ትንሽ ብዥታ ቢፈጥሩም ያሰቡትን ያህል ግን አልተሳካም። ፈጽሞ ያላናገረውን የFBI ቃል አቀባይ ጠቅሶ እንደለመደው ድምጽ ሳያስገባ “የጥቅሱ መጀመሪያ፣ የጥቅሱ መጨረሻ” በማለት አድማጭን ግራ የሚያጋባ ዘገባ ለቀቀ። እኔ እንደ ጋዜጠኛ ባይሆንም እንደ ጉዳዩ ባለቤት ከቦስተን FBI ቃል አቀባይ ግሬግ ኮምኮዊች ጋር ያደረኩት ንግግር የድምጽ መረጃ እስካሁን በእጄ ላይ አለ። በተጨማሪም እንደነ ግኡሽ ስራ ቦታው ድረስ ሄደው የFBI መርማሪዎች ካፋጠጡት ግን በሴራው አለመሳተፉ ከተረጋገጠው ቤዛ ጥላሁን ያገኘሁት ዝርዝር መረጃ ጭምር በእጄ ይገኛል።
 http://youtu.be/Zv1LtuLEFIU
ዘፋኝና የግኡሽ ደባል የነበረችው አበራሽ የማነ በግዜው የቤዛ ወዳጅ የነበረች ሲሆን አሁን ትዳር መስርተዋል። በወቅቱ ለአበራሽ የማነ መርማሪዎቹ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምንም አይነት ውንጀላ ማንም ባያቀርብባትም ፓልቶክ ላይ ብቅ ብላ በሃሰት አበበ ገላው ወነጀለኝ እንድትል ተደረገ። እነ አውራምባ ታምስም ወገንተኛ የሆነና የሚያስተዛዝብ ስራ ሰሩ። ይህንንም በወቅቱ ታዝበን አለፍነው።
FBI በዋነኛነት ትኩረት ያደረገው ግኡሽ ላይ ነበር። ለዚህም ምክንያት ደግሞ እንዳወሩት በፌስቡክ ስለተሳደበ ወይንም ስለዛተ ሳይሆን በግድያ ወንጀል ዱለታ ሊያስጠይቅ የሚችል መረጃ መርማሪዎች እጅ በመግባቱ ነበር። በቀጣይነት በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ እርምጃ የመውሰድና ያለመውሰድ መብት የመርማሪዎቹ ሲሆን የዘገባው እውነታ ግን ከላይ የተጠቀሰው ነው።
በግልጽ አፍቃሪ ወያኔ የሆነው ሄኖክ ሰማእግዜር ግን ጥቅስ ብሎ ያነበበውን ብዥታ የሚፈጥርና ከዋናው ጭብጥ ውጭ የሆነና አዛብቶ ያቀረበውን ሃተታ በተውሶ የወሰደው ከሶስተኛ ወገን፣ እንደውም እንደሰማሁት ከሆነ፣ ከትግሪኛ ዝግጅት ክፍል ነበር። ይሁንና ጥረቱ እውነቱን አልቀየረውም። ግኡሽ አበራ እኔን በስም ማጥፋት በፍርድ ቤት እንደሚከስ ወያኔዎች ደጋግመው ከመናገር አልፈው ከፍትኛ ገንዘብ ቢያዋጡም እስካሁን የተሰማ ክስ የለም።
እኔ በወቅቱ ወንጀል ሲዶልት የተደረሰበት ሰው ማንንም በስም ማጥፋት መክሰስ አይቻለውም ያልኩት እውነትን በመተማመን ነበር። አሁንም ፍርድ ቤቶች ክፍት ስለሆኑ ግኡሽ ብቻ ሳይሆን የውሸት ዘገባ በማሰራጨት እጅ ከፍንጅ በመያዝ አደባባይ ያወጣሁት ሄኖክ ሰማእግዜር (እስከ እረዳቶቹ) ዶሴውን ጠርዞ ፍርድ ቤት መሄድ ይችላል። ይሁንና ውሸት ታጥቆ አየር ላይ መውጣትም ይሁን የውሸት ዶሴ ጠርዞ ፍርድ ቤት መሮጥ ፈጽሞ እንደማያዋጣ ከወዲሁ መጠቆም እወዳለሁ።
የአሁኑ ይባስ እንዲሉ ሄኖክ አቶ ሃይለማሪያም አሜሪካ ሳይደርሱ ላስቸኳይ ስራ ተመለሱ፣ ያልደወሉትን ስልክ ደውለው ክብሩ ይቅርብኝ አሉ፣ እኔ ያልጻፍኩትን ደብዳቤ እያነበበና እያጠቀሰ፣ ያልተናገርኩትን ተናገረ፣ ያልዘገብኩትን ዘገበ እያለ ፈጽሞ ያላናገራቸውን ቃል አቀባይ ያላሉትን አሉ እያለ፣ አደባባይ ወጣ። በሁዋላ ስናጠያይቅ እንደውም የተረዳነው አሳፋሪው የቪኦኤ የሃሰት ዘገባ የተሰራው በቡድን ለሶስት መሆኑን ነው።
ታዲያ ምነው ይሄ ሁሉ የቪኦኤ ሰራዊት አንዲት ቅንጣቢ መረጃ ማውጣት ተሰናው? ከሁሉ የሚገርመው ደግሙ ውሸታችን “ቢቢጂ” የተባለ ቦርድ አጸደቀልን ብለው አይናቸውን በጨው አጥበው አደባባይ መውጣታቸው ነው። በእውነቱ በጣም ያሳዝናል። ቢቢጂም ቢሆን በመረጃ የተደገፈ ማስተባበያ ይዞ እስካልመጣ ድረስ አድማጭም አክባሪም በቀላሉ ማግኘት ይችላል ብዬ አላምንም። የተራዳሁት አንድ ጉዳይ ቪኦኤ ውስጡን ለቄስ ነው። ማንንም የመውደድም ይሁን የመጥላት ግላዊ መብታቸውን ብናከብርም ውሸት ታጥቀው አየር ላይ ከወጡ ግን ችላ ሳንል ደግመን በእውነት ሚሳኤል አናወርዳቸዋለን።
እኛ ለህዝባችን ነጻነትና መብት ከመከራከርና ከመታገል አንቆጠብም። ለዚህም ደግሞ ከማንም ፍቃድ አንጠይቅም። አንዳንድ የቪኦኤ አማርኛ ክፍል ባልደረቦች የእነ አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ክብር ተነካ ብለው እኛን ለማጥቃት መነሳታቸው ባያስገርምም ያሳዝናል። በከንቱ ይደክማሉ እንጂ አቶ ሃይለማርያምም ሆኑ አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ በዙ ተቀጣሪዎች አሏቸው። ሁለቱም ወገኖች ቪኦኤን በቃል አቀባይነትይሁን በጥብቅና አለመቅጠራቸውን በርግጠኝነት መናገር ይቻላል።
እንኳን በሜድያ ስራ የተሰማራ ጋዜጠኛ ነኝ ባይ ይቅርና ማንም እንደሚያውቀው አንድ ሚድያ ስተት ሲሰራ ባግባቡ እርማት እንዲያደርግ ይጠየቃል። ስህትት ተሰርቶ ከተገኝም አግባብ ባለው መንገድ እርምት አድርጎ ይቅርታ ይጠይቃል።። ቪኦኤን የሚያህል ግዙፍ ተቋም የሌሎችን ስራ ከማኮሰስ አልፎ በውሸት ጭብጦ የእውነትን ተራራ ለመናድ ጥረት ማድረጉ በጣም ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ከመሆን አልፎ የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ የሚለውን አባባል ያስታውሰናል።
ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ በዚህ የሀሰት ዘገባ ቁልፍ ሚና የተጫወተው ፒተር ሃይንላይን በአጠያያቂ መስፈርት ባለፈው ሳምንት ለሄኖክ ሰማ እግዜር “ሽልማት” ማቀበሉ ነው። ሄኖክም ይህንኑ ሽልማት ከአፍሪካ ክፍል ሃላፊው ከአቶ ንጉሴ መንገሻ እጅ ተቀብሏል። በርግጥ ሄኖክ ለማዛባትና ሃሰትን በይፋ በማሰራጨት ተወዳዳሪ ስላልተገኘለት ታላቅ ሽልማት ይገባው ይሆናል። ለጋዜጠኛነቱ ሽልማት መስጠት ግን ጋዜጠኝነትን መስደብ ነው።
በዚህ አይን ከፋች በሆነ አጋጣሚ ከእነ ሄኖክና ፒተር ሃይህላይን ይልቅ የአማርኛው እና የአፍሪካ ክፍል ሃላፊ የሆኑ ሁለት አንጋፋ ኢትዮጵያዊያን ጋዜጠኞችን በጣም ታዘብኩ።። ክብር ወደ ትዝብት ያለ ምክንያት እንደማይቀየር ለማንም ግልጽ ነው። ለምን ታዘብከን ብለው ከጠየቁኝ ምላሹን በዝርዝር በአደባባይ ላስረዳቸው ዝግጁ ነኝ። እስከዛው ሆድ ይፍጀው በማለት ለዛሬው የኢሳቱ ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን የቪኦኤን ከድጡ ወደ ማጡ የሆነውን የሰሞኑን ጉዞ አስመልክቶ ያዘጋጀውን ምርጥ ዝግጅት ካልሰሙት አያምልጥዎ።
መልካም አዲስ አመት ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!

የወያኔ የፖለቲካና የኢኮኖሚ እንቅስቃሲዎች ተሽመድምዷል።ትግሉም ወሳኝ ምእራፍ ላይ መሆኑ ተረጋግጧል

ወገን የሞተውን ወያኔን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የቀብር ስነ ስርአቱን የምንፈጽምበት ወቅት ላይ ነን ።
– ለስርኣቱ ቅርበት አላቸው ያሉ ምንጮች ወያኔ ወገቡ እንደተሰበረ እየተናገሩ ነው::
– ወያኔ ስልጣኑን ለህዝብ እንዲያስረክብ በተገኘው የትግል ስልት በመሳተፍ የዜግነት ድርሻችንን እነወጣ።
TPLFወያኔ እየመራው የሚገኘው ኢኮኖሚ ተሽመድምዶ ሃገርን ረመጥ ላይ እየከተታት ሲሆን የወያኔ ሳቦታጅ ጥቂት ሰዎች በሃገር ሀብት በህዝብ ላይ እንዲፈነጩ አድርጓቸዋል::በሃገሪቱ ማንኛውም አይነት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ከበፊቱ በተለየ እና በባሰ ሁኔታ ተንኮታኩተው አፈር መልበሳቸው በይፋ ታውቋል::ለስርኣቱ ቅርበት አላቸው ያሉ ምንጮች ወያኔ ወገቡ እንደተሰበረ እየተናገሩ ነው::በፖለቲካው ረገድ የስርኣቱ ገዢ ፓርቲዎች እርስ በርስ አለመተማመን ደረጃ ላይ ከመድረሳቸውም በላይ አመራሮቹ አድፍጠው አንዱን አንዱን እየጠበቀ በፍራቻ አለም ውስጥ እየዋተቱ ይገኛሉ::አቤት የሚባልበት እየጠፋ ነው፡፡ የውሳኔ ሰጪ ያለህ ቢባል መልስ አይገኝም፡፡ ፋይሎች የሚያያቸውና የሚያነባቸው አጥተዋል፡፡ መልካም አስተዳደር ገደል ገብቷል::በአላማ ሳይሆን በጊዜያዊ የመኖር ሂደት ላይ የተመሰረተው የካድሬዎቹ ሩጫ ድካምን በመፍጠሩ ሁሉም በያለበት ቆም ብሎ እያሰበ ሲሆን አሳቡም የገፈፍኩትን ገፍፌ ሃገርን ድባቅ መትቼ ልሽሽ ሆኗል::
ገበናን ገበና ይገፈዋል እንደሚባለው የወያኔ ጁንታ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ የገነባው ኢኮኖሚያዊ ገበና በገበና ተጋልጧል:: የማይሰማ ነገር የለም እና እኛም ሰማን አነበብን አየንም እነሆ ታዝበን ዝም አላልንም ገበናዎቹ ገበናውን ሲገልቡት አብረን አልሳቅንም ሀገር ነውና ገበናዎቹን ተመርኩዘን የምንለውን ልንል ይኸው ተከሰትን::
የስርኣቱ ቅርብ ምንጮች የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በመሽመድመዱ ወያኔ ወገቡ መቆረጡን እና መምራት አለመቻሉን በለሆሳስ በመተንፈስ ኢኮኖሚው መንኮታኮቱን ሲናገሩ የንግድ ስራዎች ከፓርቲ ድርጅቶች ውሽ በታም ተዳክመው እና ሞተው ያሉ ሲሆን የገንዘብ እንቅስቃሴዎች ጭራሽ ገደል መግባታቸውን እና ደንበኞች በባንኮች ላይ ያላቸው አመነታ በመጥፋቱ ግንኙነቶች መልፈስፈሳቸው በይበልጥ ለግል ባንኮች መዳከም ምክንያት ሆነዋል ሲሉ ይህ ደሞ አሉ የገንዝብ እንቅስቃሴውን ገድሎታል:: ምንሊክ ሳልሳዊ በጣም ድብን ያለ እውነት ነው::በውጭ ምንዛሪ ችግርና እጥረት ምክንያት በጣም የሚያስፈልጉ ዕቃዎች እንደተለመደው ከውጭ እየገቡ አይደለም፡፡ በጥቂቱ የመጡ ካሉም ዋጋቸው የማይቻል እየሆነ ነው፡፡ ብለውም አክለው አስቀምጠዋል::
ወያኔ አስፈላጊውን ገንዘብ ባለማግኘቱ ፕሮጀክቶች የቆሙ የተጓተቱ ሲሆን የሚሰበከው እድገት ለፕሮፓጋንዳዊ የሚዲያ ፍጆታ ብቻ መሆኑ ተረጋግጧል::ወያኔ የፋይናንስ ጥያቄውን ሊጨብጠው አይደለም ሊዳስሰው አልቻለም::በኢንቨስትመንት እንሰማራለን ብለው የመጡ የውጭው አለም ሰዎች በቢሮክራሲው መንተክተክ የተነሳ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ ትብብር ማግኘት አለመቻላቸውን ከመናገራቸውም በላይ የጀመሩት ኢንቨስትመት እንደሚቋረጥ የወያነ ባለስልጣናት እንደሚያስቆሟቸው እና ለምን ሲሉ መልስ የሚሰጣቸው አከል እንደሌለ እና ጨረታ ካሸነፉ በኋላ እንደሚሰረዝ ለማን እንደሚሰጥ እንደማያውቁ አማረው እየተናገሩ ነው::
ሌላው የሃገር ውስጥ ታዋቂ ነጋዴዎችን ጨምሮ የወያኔ ባላባቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እያሸሹ መሆኑ ነው::የተረፈ ካለ ደሞ ወደ ባንክ ከመውሰድ ይልቅ ቤጅ መያዝ እየተመረጠ መቷል::አገር ውስጥ ደሞ ከማስቀመጥ ይልቅ ውጪ አገር መላክ እየተለመደ መቷል::ምንሊክ ሳልሳዊ አገር ውስጥ ባለው የውጭ ምንዛሪ ክምችት ላይ ተጨማሪ ጉልበት ሊፈጥር የሚገባው የውጭ ምንዛሪ ግኝትም ውጭ እንዲቀር እየተደረገ ነው፡፡ የገባ ካለም በጥቁር ገበያ እንደገና እንዲወጣ እየተደረገ በመሆኑ አገሪቱ ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም፡፡ብለዋል የስርኣቱ ታማኞች:; ይህ የሚያመለክተው ዜጎች በፖለቲካው ጉዞ ላይ እምነት እንዳሌላቸው ሲሆን እየተሽመደመደ እና እየደቀቀ ያለው የፖለቲካ ስራቲ ምንም ለውጥ ሊያመጣ አለመቻሉ ሰዎች በወንጀለኝነት ሳይሆን በአስተሳሰባቸው ወህኒ መውረዳቸው የፈጠረው ስጋት ነው::
ዜጎች በህግ ላይ እና በንጽህናቸው ላይ ከመተማመን ይልቅ የህግ የበላይነት ከመጥፋቱ አንሳር እጅግ ፍርሃት ውስጥ በመግባታቸው የተማሩ እና በንግዱ አለም የተሰማሩ ሁሉ አፍርሃት ከመርበድበዳቸው እና ከመሰደዳቸው በላይ አሉ የተባሉትም ወያኔ በሙስና ባልደረቦቹ ላይ ፖለቲካዉ ገጀራ ሲያሳርፍ እየተመለከቱ ስራ በማቆም ከመደናበራቸውም ሌላ በራሳቸው አለመተማመን ያለባቸውን ጨምሮ በሙስናው ከባለስልጣናት ጋር የተነከሩ ሲሆን ሌሎች ደሞ እስከሚጣራ ለምን ልታሽ በሚል ባለው የፖለቲካ አመራሩ ላይ እምነት በማጣት የንግዱን ስራ ገለውት ከሃገር በመሸሽ ላይ ናቸው::
የተጭበረበረ አፋኝ ፖለቲካ ያስከተለው የኢኮኖሚ መንኮታኮት የአገሪቱን የፖለቲካ አናቶች ለውጥ እንዳያመጡ በመተብተብ ቀውስ ውስጥ የከተታቸው መሆኑን ከስብሰባዎች እና ከጭብጨባዎች ብዛት እየታዘብን ነው::በሌላ በኩል ሚዲያዎች ህዝብን መዋሸታቸው እና ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ መዋላቸው አገሪቷ እንድትንኮታኮት በር የከፈተ ሲሆን የዚህ መፍትሄ ስልጣን መልቀቅ ነው::ወያኔ ስልጣኑን ልህዝብ እንዲያስረክብ በተገኘው የትግል ስልት በሙሉ በመሳተፍ የዜግነት ድርሻችንን እነወጣ።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

lørdag 13. september 2014

በቦረና ዞን ነዋሪ የሆኑት አቶ ጎንፋ አበራ ከፖሊስ በተተኮሰ 4 ጥይት ሕይወታቸው አለፈ

አስከሬኑ ሽኝት ላይ የነበሩ የአባያ ገላና ወረዳ ሰብሳቢ አቶ በድሉ መንግሥቱ በፖሊስ ተደብድው በእስር ላይ ናቸው
(ፍኖተ ነፃነት) በቦረና ዞን ገላና ወረዳ ቶሬ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጎንፋ አበራ ጳጉሜ 4 ቀን 2006 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ወታደር ዋቆ ሁቃ በተባለ ፖሊስ በተተኮሰ 4 ጥይት ህይወታቸው ማለፉን የቦረና ዞን የአንድነት አስተባባሪ አቶ ጌታቸው በቀለ ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ የአቶ ጎንፋ አስከሬን ወደ ቶሬ ከተማ ጤና ጣቢያ ተወስዶ ሐሙስ መስከረም 1 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ቤተሰባቸው ወደሚገኝበት አምቦ ከተማ ሲሸኝ የቶሬ ከተማ ነዋሪዎች አሸኛኘት ያደረጉ ሲሆን የአባያ ገላና ወረዳ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ በድሉ መንግሥቱ ከሽኝቱ ሲመለሱ በፖሊስ ተይዘው ድብደባ ከተፈጸመባቸው በኋላ በእስር ላይ መሆናቸውን አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡ አቶ በድሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ በተደጋጋሚ በገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ድብደባና እስር ይፈጸምባቸው የነበረና ባሳለፍነው ዓመትም ይሰሩበት የነበረ የግል ታክሲያቸውን በድንጋይ የሰባበሩባቸው ሲሆን አቶ በድሉና በአካባቢው ያሉ የፓርቲው አባሎች ግን እየደረሰባቸው ያለው ዛቻ፣ ማስፈራሪያና እስር ከትግሉ ፈቀቅ እንደማያደርጋቸው ሰላማዊ ትግሉንም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡ ወደ ቶሬ ወረዳ ፖሊስ ደውለን ሁኔታውን ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡
Car ethiopia
Car ethiopia1

2007 ወሳኝ የትግል ዓመት!!!


ሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ ምህረት ለኛ ለኢትዮጵያዊያን በአብዛኛው በመጥፎ የሚታወስ ዓመት ነው። 2006፣ በመካከለኛው ምስራቅም ሆነ በአፍሪቃ በስደት ላይ የሚገኙ ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ዓመት ነበር። 2006፣ ቀደም ባሉ ዓመታት አገራቸዉን ለቅቀዉ የተሰደዱ ሳይደላቸው በርካታ አዳዲስ ስደኞች ከአገር ወጥተው በበረሃዎችን ቀልጠው፤ በባህር ሰጥመው ያለቁበት አሳዛኝ ዓመት ነው። 2006፣ ጥንቃቄ በተሞላበትና በተቆጠበ መንገድም ቢሆን የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙ ወገኖቻችን ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006፣ በአምቦ፣ በለቀምት፣ በጅማ በሀረር በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተገደሉበት፤ በአስር ሺዎች የሚገመቱት ደግሞ የታሰሩበት ዓመት ነው። 2006፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባና አካባቢው በ100 ሺዎች የሚገመት ኢትዮጵያዊ የተፈናቀለበት ዓመት ነው። 2006 ቁጥራችው ቀላል ያልሆኑ የነፃነት ታጋዮች ከጎረቤት አገራት ታፍነው ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006 የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በጉዞ ላይ እያለ በትራንዚት አውሮፕላን ለመቀየር ባረፈበት በየመን ዋና ከተማ ሰንዓ በየመን መንግሥት ወንበዴዎች ታፍኖ ለሸሪካቸው ህወሓት በህገወጥ መንገድ አስተላልፈው ለስቃይ እንዲዳረግ የተደረገበት ዓመት ነው። በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ነው 2006 “ጥቁር ዓመት” የሚል ስያሜ ያገኘው።
ጭንቅላት የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው ድኩማን ሰላዮችና ፈንጋዮች የመጨረሻውን የመንግሥት ሥልጣን የያዙበትና ውሳኔያቸው “እሰረው፣ ክሰሰው፣ ግረፈው፣ ግደለው …” ብቻ የሆነበት ዓመት መሆኑ የ2006 ልዩ መታወቂያው ሆኖ ይቆይ ይሆናል። ይሁን እንጂ በ2006 ጨለማ ውስጥ የታዩ የብርሃን ጨረሮችም እንደነበሩና እንዳሉም መርሳት አይገባም።
በሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ ምህረት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመቸውም በላይ በህወሓት አገዛዝ አምርሯል፤ በሁለገብ ትግል የህወሓትን አገዛዝ ለመፋለም የቆረጡ ወገኖች ትብብር ተጠናክሯል። በ2006፣ ኢትዮጵያ ዉስጥም ከኢትዮጵያም ውጭም የንቅናቄዓችን የግንቦት 7 ድርጅታዊ መዋቅር ተጠናክሯል። በ2006፣ ከህወሓት አገዛዝ ጋር ያለው መፋጠጥ ከሯል። እነዚህ ሁኔታዎች 2007 አገራችን በለውጥ ማዕበል የምትናጥበት ዓመት ሊሆን እንደሚችል ያመለክታሉ።
በአዲሱ ሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ትልቁ ሥራ ድርጅታዊ አቅምን ማጎልበት ነው። በተለይ ወጣቶች በአምባገነን ሥርዓቶች ውስጥ ሕዝባዊ የትግል ድርጅቶችን እንዴት መመሥረት እንደሚቻል ማጥናት እና መፈተሽ ይኖርባቸዋል። ትናንሽ የግንቦት 7 ድርጅታዊ ቋጠሮዎች በመላው አገሪቱ መሠራጨት ይኖርባቸዋል። ወጣቶች ትናንሽ ኢ-መደበኛ ስብስቦችን ቶሎ መፍጠር እና አደጋ ሲያጋጥም ቶሎ ማፍረስ መልመድ ይኖርባቸዋል። ይህንን ክህሎት ደግሞ በቀጥታ ከሌሎች አገራት ከመዋስ ሀገር በቀል ቢሆን ይመረጣል።
በሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የጽዋ ማኅበሮች፣ መድረሳዎችና ጀማዎች፣ የስፓርት ቡድኖችና ደጋፊዎች፣ የመንደር ደቦዎችና የቡና ተርቲቦች፣ ስም ያላቸውም፣ ስም የሌላቸውም ስብስቦች የግንቦት 7 አባላት መገናኛዎች ይሆናሉ። በ2007 የግንቦት 7 አባል መሆን የምርጥ ዜግነት ምልክት መሆኑ በስፋት ተቀባይነት የሚያገኝበት ዓመት ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። በ2007 በህወሓት ካድሬዎች “ሽብርተኛ” መባል የሚያስደስትና እንደ ሽልማት ተደርጎ የሚወሰድበት ዓመት ይሆናል ብለንም ተስፋ እናደርጋለን። በ2007 እስር ማስፈራሪያ መሆኑ ያከትማል። በ2007 የኢትዮጵያ ወጣቶች በአርበኝነታቸው ይታወቃሉ። በ 2007 እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የህወሓት ሹማንምትን ዘረፋ የሚያጋልጥበት ዓመት ይሆናል። 2007 ዳኞች “እንቢ፣ በሀሰት አንፈርድም”፤ የመንግሥት ጋዜጠኖች “እውነቱን ደብቀን አንዋሽም”፤ ፓሊሶች “ወገናችንን አንደበድብም፣ አናስርም፣ አንገርፍም”፤ ወታደሮች ደግሞ “በወገናችን ላይ አንተኩስም” የሚሉበት ዓመት ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
በዚህም ምክንያት 2007ን የምንቀበለው በታላቅ ተስፋና ዝግጅት ነው። በ 2007 ነፃነትና አምባገነንነት፤ ዘረኛነትና አንድነት፤ እውነትና ውሸት፤ አድርባይነትና አርበኝነት፤ ዝርፊያና ንጽህና፤ ድህነትና ብልጽግና የሚፋጠጡበት ዓመት ይሆናል ብለን እንጠብቃለን። በአጭሩ 2007 የወሳኝ ትግል ዓመት ይሆናል።
ሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የኢትዮጵያ መፃዒ እድል የሚወሰንበት ዓመት በመሆኑ ሁላችንም በተነሳሳ የአርበኝነት መንፈስ እንድንቀበለው ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪ ያደርጋል።
መልካም አዲስ ዓመት!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

fredag 12. september 2014

የማይዝሉ ጀግኖች! (በላይ ማናዬ)

ጫማ ማውለቅን ጨምሮ እጅግ አሰልቺና አሳቃቂ የሆነውን ፍተሻ አልፈን ወደ ውስጥ ዘለቅን፡፡ በጋራ ሰብሰብ ብለን ወደ ስፍራው ካቀናነው ወጣቶች መካከል ግማሻችን በዞን አንድ ሌሎቻችን በሌላኛው ዞን ተከፋፍለን ወደ ወዳጆቻችን ገሰገስን፡፡

አሁን ያለነው በፌደራል መንግስቱ ስር ከሚተዳደሩት እስር ቤቶች መካከል አንዱ በሆነው ቂሊንጦ ውስጥ ነው፡፡ እዚህ እስር ቤት ውስጥ ልናያቸው የናፈቅናቸው የአርነት ታጋዮች፣ የብዙሃን ድምጾች አሉ፡፡ ከሁለቱ ቡድኖች ከአንደኛው ጋር በመቀላቀል ወደጀግኖቹ አመራሁ፡፡ ከፊት ያሉት ቀድመው አስጠርተዋቸው ኖሯል፡፡ ሁሉም በፈገግታ ታጅበው ከአጥሩ ማዶ ሰላምታ ሰጡን፡፡ ውብ በሆነ ፈገግታና የናፍቆት ስሜት ውስጥ መሆናችን ከጠያቂዎችም ከተጠያቂዎችም በኩል በጉልህ ይታያል፡፡
10616558_581452168647112_4041948437710460738_n
በቀጭን ሰውነቱ ላይ ስስ ነጭ ቲሸርት ለብሶ ሲታይ በእድሜ በጣም ለጋ አስመስሎታል፡፡ ረጂም ቁመቱ ደግሞ ቅጥነቱን አጉልቶታል፡፡ ፍልቅልቅ ነው፤ ሙሉ ደስተኛ ገጽታው ማንንም ቢሆን በፍጥነት የሚያላምድ ይመስላል፡፡ ሲናገር የሚደመጥ፣ ሲናገሩ የሚያደምጥ ግሩም ወጣት ነው፡፡ ይህ ወጣት የዞን 9 ጦማሪያን ቡድን አባልና በ2006 ዓ.ም የቡድኑ አስተባባሪ የሆነው ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ነው፡፡ ሌሎች አብረውኝ የነበሩት ወጣቶች ከሌሎች ሁለት ታሳሪ ጋዜጠኞች ጋር እያወሩ ሳሉ እኔ ከናቲ ጋር አንዳንድ ጉዳዮችን እያነሳን እያለ ስለወቅታዊ አያያዛቸውና ስላለፈው ሁኔታ ወደ ኋላ መለስ ብዬ ጥያቄዎችን አነሳሁለት፡፡ ‹‹ሀገሬ ላይ እርግጠኛ የሆንሁበት ጉዳይ ቢኖር እኔን እንደ ዜጋ የሚጠብቀኝ መንግስት የሌለኝ መሆኑን ነው፡፡ ህገ-መንግስቱ አልጠበቀኝም፡፡ ህገ-መንግስቱ ጥሩ ቢሆንም አልተከበረም›› አለኝ ወጣቱ ጦማሪ፡፡
በ2006 ዓ.ም ሚያዚያ ወር አጋማሽ ላይ ነበር መንግስት የዞን 9 አባላትን ለቃቅሞ ወደ ማዕከላዊ ማጎሪያ ያጋዛቸው፡፡ የጡመራ ቡድኑ አባላት በሽበር ወንጀል ተጠርጥረው እንደታሰሩ ተገልጾላቸው ለረጂም ጊዜያት በምርመራ ላይ መደበኛ ክስ ሳይመሰረትባቸው ከቆዩ በኋላ፣ መደበኛ ክሱ ሲመሰረት ‹ከሽብር ቡድኖች ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ ህገ-መንግስቱን በኃይል ለመናድ…› በሚሉ ‹ወንጀሎች› ተከሰው በቂሊንጦ እስር ቤት ሆነው የፍርድ ሂደታቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ፡፡ ከቡድኑ አባላት መካከል ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ አጥናፍ ብርሃኔ እና ዘላለም ክብረት እንዲሁም አብረው በተመሳሳይ ክስ የተያዙት ሁለቱ ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ በዚሁ በቂሊንጦ ሲገኙ ጦማሪት ማህሌት ፋንታሁን እና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ ደግሞ ቃሊቲ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡
እነዚህን እና ሌሎች ቀደም ብለው በእስር ላይ የሚገኙትን ጋዜጠኞች፣ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኪሚቴ አባላትን፣ ፖለቲከኞችን እና ሌሎችንም ታሳሪዎች 2007 ዓ.ም አዲስ አመት መባቻን አስመልክተን ወጣቶች ሰብሰብ ብለን በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት ጠይቀናቸው ነበር፡፡ በተለይ ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ሚዲያው ‹‹ጥቁር ሳምንት›› (black week) በሚል ለአምስት ቀናት ዘመቻ (campaign) በተካሄደ ጊዜ በዘመቻ መጨረሻው ቀን የዘመቻው አስተባባሪዎች አዲስ አመትን በማስመልከት ‹አዲስ አመት በዓልን ከነጻነት ታጋዮች ጋር› በሚል የታሰሩ የነጻነት ታጋዮችን እንድንጠይቅ ጥሪ ማስተላለፋቸውና ጥሪውን የተቀበሉ ወጣቶች መበርከት የእስረኞችን የጥየቃ ፕሮግራም ልዩ አድርጎት ነበር፡፡
እስር ቤት ታጉረው የሚገኙ የነጻነት ታጋዮችም በወጣቶቹ ድርጊት እጅግ መደሰታቸውን በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ እኒያ የማይዝሉ ጀግኖች እስክንድር ነጋና አንዱዓለም አራጌ በቃሊቲ በተገኘንበት ወቅት በወጣቶቹ ድርጊት እንደኮሩና ትግሉ እንዳልቆመም ማሳያ መሆኑን ከመግለጽ አልተቆጠቡም፡፡ ‹‹እኛ ገና በሰላማዊ ትግሉ ጅማሮ ላይ ነው የታሰርነው፡፡ ትግሉ ገና መጀመሩ ነው፡፡ ትግሉ በተግባር የሚፈትናቸው በርካታ ጀግኖች አሉ›› ሲል ነበር ትንታጉ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ እስክንድር ነጋ ወጣቶችን ያበረታታው፡፡
እስክንድር የታሰረ አይመስልም፡፡ አልታሰረምም! በእስር ቤቱ ፖሊሶችና በአንድ ሲቪል በለበሰ ጆሮ ጠቢ ታጅቦ ወደ እኛ ቢቀርብም እስክንድር ፍጹም ነጻ ሆኖ ነበር የሚያወራን፡፡ እስክንድር ነጋን ይፈሩታል እንጂ እሱ አይፈራቸውም፡፡ ይህንን ደግሞ በተግባር ያሳየ ጀግና ነው፡፡ ‹‹አንተ እኮ የምንግዜም ጀግናችን ነህ፤ እንኮራብሃለን!›› አለው ከመካከላችን አንዱ፡፡ እስክንድር መለሰ፤ ‹‹ለእኔ ደግሞ እናንተ ከውጭ ያላችሁ ወጣቶች ናችሁ ጀግኖቼ!››
የእስክንድር መንፈስ ወደ ሌሎች የመጋባት ኃይል አለው፡፡ የዞን 9 የጡመራ ቡድን አባላት የጥንካሬ ምንጭ ይህ የማይዝል ጀግና እስክንድር ነጋ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ቂሊንጦ በነበርንበት ወቅት ፍልቅልቁ ወጣት ናትናኤል የሚያረጋግጠውም ይህንኑ ነው፡፡ ‹‹ያኔ ወደ እስር ቤት ሳንገባ በፊት እስክንድር ነጋን ልንጠይቅ ቃሊቲ ስንሄድ እስክንድር ሁሌም ይገርመን ነበር፡፡ ሁሌም ጠንካራ፣ ደስተኛና አስተዋይ ሆኖ ነበር የምናገኘው፡፡ እና፣ እሱን እያየን መታሰር፣ መስዋዕትነት መክፈል ሌላውስ ለምን ይፈራል ታዲያ ስንል ራሳችንን እንጠይቅ ነበር፡፡ እስክንድር ልዩ ሰው ነው፤ የሚጋባ መንፈስ ያለው ጀግና!››
ተስፋለም፣ ናትናኤል፣ አስማማው እና ሌሎችንም ወጣቶች ‹‹እስክንድር አክብሮቱን ገልጾላችኋል እኮ፤ ሰምታችኋል?›› ሲባሉ በደስታ አወንታዊ ምላሽ ሰጡ፡፡ እስክንድር ጀግኖችን የሚያፈራ ጀግና ነው፡፡ ዛሬ ሌሎች ወጣት የአርነት ንቅናቄው የማይዝሉ ጀግኖች የአርዓያቸው እስክንድርን ቃል ለሌሎች ሲናገሩ ይደግሙታን፡፡ ወጣቱ ጦማሪ ናትናኤል ከቂሊንጦ ተናገረ፣ ‹‹ለሀገር የሚያስቡ ብዙ ወጣቶች በየጊዜው ማበባቸው አይቀሬ ነው፡፡ እየታየ ያለውም ይሄው ነው፡፡ ምንግዜም የሚበረቱ ሰዎች ለውጥ ያመጣሉ ብዬ አምናለሁ፡፡››
የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆነው ያሲን ኑሩ ደግሞ እዛ ቂሊንጦ እስር ቤት ልንጠይቅ ለሄድነው ወጣቶች እንዲህ አለን፤ ‹‹መንግስት በኃይማኖቶች መካከል ልዩነት መፍጠር ይፈልጋል፡፡ እናንተ ክርስቲያኖች የኃይማኖት ድንበር ጥሳችሁ ከእኛ ከሙስሊም ወንድሞቻችሁ ጋር መቆማችሁን እናደንቃለን፡፡ እኛን ለመጠየቅ እስር ቤት ድረስ ስለመጣችሁ በጣም እናመሰግናለን፡፡ ትግሉ ከዚህም በላይ መስዋዕትነት ያስከፍላልና በርቱ፡፡››
ከሁሉም ታሳሪዎች አንደበት የሚወጣው መልዕክት አስገራሚ ነው፤ ሊያበረታቸው ወደ እነሱ የሚሄደውን ጠያቂ ሁሉ መልሰው አበርትተው ይልኩታል፡፡ እነሱ የማይዝሉ ጀግኖች ሆነው የዛለውን የሀገሬ ወጣት ‹‹በርታ!›› ይሉታል፡፡ አጠር ቀጠን ያለ ቆፍጣና ወጣት ነው፤ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ፡፡ ‹‹በጥቁሩ ሳምንት ዘመቻ ያደረጋችሁትን ነገር ሰምተናል፡፡ በጣም ደስ የሚል ስራ ሰርታችኋል፡፡ መጥታችሁ ስለጠየቃችሁን ደስ ብሎናል፡፡ እስሩ ቀጣይነት እንደሚኖረው ቢታወቅም፣ በየትኛውም ሁኔታ በርታትችሁ እንድትቀጥሉ እፈልጋለሁ›› ሲል እሱም የማበረታቻ ቃሉን ተናገረ፡፡
ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌ በበኩሉ የማሃተመ ጋንዲን የሰላማዊ ትግል አስተምሮ በምሳሌነት ሲያነሳ ከቆየ በኋላ፣ እሱን አብነት አድርገን በሰላማዊ ትግላችን እንድንበረታ አሳሰበን፡፡ ‹‹የሁላችንም ተስፋ ያለው እዚህ እስር ቤት አይደለም፡፡ ከዚህ ውጭ ካላችሁት ነው ሁሉም ነገር ያለው፡፡ በርቱ! ኢትዮጵያ እንደ እናንተ ያሉ እጅግ ብዙዎችን ትፈልጋለች፡፡ ደግሞም አሉ! በበዓል ቀን ስለመጣችሁና ስለጠየቃችሁን ኮርተንባችኋል፡፡››
ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የባለሙያ እጥረት እጅጉን እንደሚያሳስበው ይናገራል፡፡ በእስር ላይ ካለ ጀምሮ የሚያየው የባለሙያ እጥረት ሳይታሰር በፊት ከሚያውቀው በላይ ሳይሆንበት አልቀረም፡፡ ‹‹ታስሬ ባለሁባቸው ቀናት ሁሉ የታዘብኩት ነገር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የባለሙያ እጥረት በሁሉም ዘርፍ መኖሩን ነው፡፡ አቅም ያላቸው ዜጎች ከስርዓቱ በመገፋታቸው ክፍተቱ እንዲሰፋ ሆኗል፡፡ በጣም ነው የሚያሳዝነው፤ የሚሰሩ ሰዎች በተገቢው ቦታ ላይ አለመኖራቸውን አይቻለሁ፡፡ የሚያሰራ ስርዓት ስለሌለ ብዙዎች ህሊናቸውን መርጠው በመራቃቸው ይመስለኛል አቅም ያላቸው ሰዎች የራቁት፡፡ ይህ ለሀገር አሳሳቢ ነው፡፡››
ለመሆኑ በተለየ ሳላከናውነው (ወይም እንደ ቡድን ሳናከናውነው) በመታሰሬ እቆጫለሁ የምትለው ነገር ይኖር ይሆን ስል ጥያቄ አነሳሁለት፡፡ ‹‹የሚቆጨኝ ነገር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ተቋማት በእንግሊዝኛ የተሰሩ የጥናት ስራዎችን በመምረጥ አሰባስበን በአማርኛ ቋንቋ በጆርናል መልክ ለመስራት አስበን ያን ሳንሰራ በመታሰራችን ነው›› አለኝ ትክዝ ባለ ስሜት፡፡ ሆኖም አለ ናትናኤል፣ ሆኖም ‹‹አሁን በተለያዩ ሁኔታዎችና ጉዳዮች ላይ ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያው በኩል የሚሰሩ ስራዎች እንዳሉ ስሰማ በጣም ነው ደስ ያለኝ፡፡ እኛን አስረው ሌላው ዝም እንዲል ፈልገው ኖሮ ከሆነ እንዳልተሳካላቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ለሀገር የሚያስቡ ብዙ ወጣቶች በየጊዜው ማበባቸው አይቀሬ ነው፡፡ እየታየ ያለውም ይሄው ነው፡፡ ምንግዜም የሚበረቱ ሰዎች ለውጥ ያመጣሉ ብዬ አምናለሁ›› አለ ቀጭኑ ቁምነገረኛ ወጣት፡፡
በግሌ እንደዘንድሮ አይነት አዲስ ዓመት በማይረሳ መልኩ ያሳለፍኩ አይመስለኝም፡፡ ከእነዚህ ባለብሩህ አዕምሮ ባለቤቶች፣ ሰላማዊ ታጋዮች፣ ሀገር ወዳዶች ጋር በዓልን ከማሳለፍ የበለጠ ምን ደስ የሚያሰኝ ነገር ይኖራል!
እናንተ የማትዝሉ ጀግኖች…የእናንተን ፈር በሚከተሉ እልፍ ኢትዮጵያውያን ነገ ብሩህ ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊና የዘመነ አስተዳደር ይገባታል!

onsdag 10. september 2014

የዘ-ሐበሻ አንባቢያን የዓመቱ ምርጥ ሰው ይፋ ሆነ

ነጻነት፣ ፈጣሪ ለሰው ልጆች ሁሉ በነጻ የሰጠን ገጸ በረከት ነው። ነገር ግን በአገራችን ኢትዮጵያ፣ ጥቂቶች፣ የያዙትን መሳሪያና ያላቸዉን ጡንቻ በመጠቀም፣ ነጻነታችንን ሰርቀዉን፣ በባርነትና በፍርሃት እንድንኖር አድርገዉናል። ከፍርሃት የተነሳ ብዙዎቻችን ከአገር ተሰደናል። ብዙዎቻችን በአገራችን እንደ ሁለተኛና ሶስተኝ ዜጎች ተቆጠረን፣ አንገታችንን ደፍተን፣ በሉ የምናብለውን እያልን፣ ሰልፍ ዉጥ ስንባል ሰልፍ እየወጣን፣ ከፍቃዳችን ዉጭ የጥቂቶችን ፍላጎት ብቻ እየፈጸምን የምንኖር አለን። በፍርሃት ተተብትበንና በጥቅም ታስረን።
person of the year
በሌሎች ትግልና መስዋእትነት ነጻነታችንን ማግኘት የምንፈልግ ጥቂቶች አይደለንም። ነጻነትን ፈልገናት፣ ግን ለነጻነት የሚከፈለዉን ዋጋ ለመከፈል ፍቃደኝነት አይታይብንም። ከታሰርንበት ፍርሃት ለመላቀቅ አልቻልንም።
ነገር ግን ከመቼውም ጊዜ የበለጠ፣ የፍርሃትን ቀንበር በመስበር፣ ለራሳቸው ነጻነትን አዉጀው፣ ለሌሎች መብት የተሰለፉ ብዙ አኩሩ ልጆችን ኢትዮጵያ እያፈራች ነው። እስራትን፣ እንግልትን የማይፈሩ፣ ለአገራቸዉን ለሕዝባቸው መስዋእትነት ለመክፈል የተዘጋጁ፣ ጠመንጃና ጥይት ሳይዙ ጀግንነት ምን ማለት እንደሆነ ያስመሰከሩ ልጆች !
ከነዚህ አኩሪ የኢትዮጵያ ልጆች መካከል፣ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆነው፣ ታዋቂው ጦማሪ፣ ወጣት አብርሃ ደስታ ይገኝበታል። ወጣት አብርሃ ፣ ከሕወሃት አፍንጫ ሥር ሆኖ ፣ ብዙዎች ያላወቁትንና ያላዩትን፣ በትግራይ ባሉ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለዉን ግፍና ጭቆና ሲታግልና ሲያጋልጥ የነበረ ወጣት ነው። ብዙ ጊዜ በሕወሃት ካድሬዎች ተደብድቧል። ተሰድቧል። ዛቻና ማስፈራራት ደርሶበታል። ነገር ግን አብርሃ አልተበገረም። አንዳንዶች እንደሚያደርጉት፣ የሕወሃት አባልና ካድሬ ሆኖ በግሉ የተለየ ጥቅም ሊያገኝ ይችል ነበር። በጥቅም ሊደልሉት ሞክረዋል። ነገር ግን ራስ ወዳድ አልሆነም። ከግል ጥቅም ይልቅ የአገርን እና የሕዝብን ጥቅም አስቀደመ። የህዝቡን ብሶት እያነሳ ጮኸ።
አገራችን ኢትዮጵያን ትልቅ ስጋት ላይ ከጣሉት ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ በሕወሃት/ኢሕአዴግ የተዘረጋው የዘር ፖለቲካ ነው። አገዛዙ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ … እያለ ዜጎችን በመከፋፈል ፣ አንዱን ከአንዱ ጋር በማጣላት፣ ለብዙ ወገኖች እልቂትና መፍናቀል ምክንያት ሆኗል። አብርሃ ደስታ « ብሄሬ(ዘሬ) ኢትዮጵያዊነት ነው» በሚል ዜጎችን በዘራቸው ሳይሆን በስራቸው ብቻ መመዘን እንዳለባቸው የሰበከ፣ በነአጼ ዮሐንስ እና ራስ አሉላ አባ ነጋ መንፈስ፣ የኢትዮጵያዊነትን ደውል ያቃጨለ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጅ ነው።
ሐሳብ፣ ጽሁፍን መመከት የማይችሉ፣ የጫካ ፖለቲካ የሚያራምዱ ሕወሃቶች ግን ፣ ትችቶችን ተቀብለው ማሻሻያዎችን ከማድረግና የሕዝብ ጥያቄ ከማዳመጥ ይልቅ፣ እንደለመዱት የሚቃወሟቸውን መጨፍለቅ መረጡ። ሐምሌ አንድ ቀን 2006፣ አብርሃ ደሳታን እየደበደቡ አሰሩት። ከመቀሌ ወደ አዲስ አበባ ማእከላዊ ወሰዱት። በሽብርተኝነት ክስ ከሰሱት። ፖሊስ «መረጃ እስካሰባሰብ» ብሎ የ28 ቀን ቀጠሮ ጠየቀ። «ፍርድ ቤቱ» ግን መረጃ ሳያይ፣ የፖሊስን ጥያቄ ተቀበሎ፣ የአብርሃን የዋስታና መብት ረግጦ፣ ለነሐሴ 29 ቀጠሮ ሰጠ። በቀጠሮ ቀን፣ አሁንም ፖሊስ ማስረጃ ያቀርባል ተብሎ ሲጠብቅ እንደገና ተጨማሪ 28 ቀን መረጃ ለማሰባሰ ጠየቀ። ፍርድ ቤቱ እንደገና ሁለተኛ ቀጠሮ ለመስከረም 22 ሰጠ። አብርሃ ደሳታ፣ ምንም አይነት መረጃ ባልቀረበበት ሁኔታ ይኸው ፣ በማእከላዊ እሥር ቤት እየማቀቀ ይገኛል።
አብርሃ ደስታ ሊታሰር እንደሚችል ያውቅ ነበር። ነገር ግን የዜጎችን የነጻነት ጥያቄ፣ ጥቂቶች አፍነው ማቆየት እንደማይችሉ በመረዳቱና፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች፣ ምሳሌ አግኝተው፣ ይበረታቱ የዘንድ፣ የትግል ቁርጠኝነትን ያሳየው።
የኢትዮጵያን ትንሳኤ ለማየት፣ እንደ አብርሃ ደስታ ያሉ በየክልሉና በየቦታው በብዛት መነሳታቸው አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት፣ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በያለንብት የአብርሃ ደስታን ፈለግ ተከትለን፣ ለሕግ የበላይነት ፣ ለሰብአዊ መብት መከበር፣ ለነጻነት፣ ለኢትዮጵያነት እንቆም ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን። ላባረከተው ትልቅ አስተዋጾ፣ ላሳየው ቁርጠኝነት፣ ከአንባቢያኖቻችንም ብዙ ባገኘው ብዙ ድምጽ መሰረት፣ አብርሃ ደስታን የ2007 የዘ-ሐበሻ አንባቢያን የዓመቱ ሰው መሆኑን ስናሳወቅ በታላቅ አክብሮት ነው።
በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ የምንኖር ኢትዮጵያዉያን ሁሉ መልካን እንቁጣጣሽ እየተመኘን ፣ 2007 የለወጥ፣ የሰላም፣ የነጻነት አመት እንዲሆንልን ምኞታችንን እንገልጻለን።

አዲሱን ዓመት በማስመልከት ከነጻነት ታጋዮች ጋር በቂሊንጦ እስር ቤት

ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ሚዲያው ‹‹ጥቁር ሳምንት›› (black week) በሚል ለአምስት ቀናት ዘመቻ (campaign) መካሄዱ ይታወሳል፡፡ በዚያ የጥቁር ሳምንት ዘመቻ ወቅት በመጨረሻው ቀን አስተባባሪዎቹ አዲስ አመትን በማስመልከት ‹አዲስ አመት በዓልን ከነጻነት ታጋዮች ጋር› በሚል የታሰሩ የነጻነት ታጋዮች እንዲጠየቁ ጥሪ መተላለፉ አይዘነጋም፡፡ በመሆኑም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ዝግጅት ክፍል ጳጉሜ 5 ቀን 2006 ዓ.ም በቂሊንጦ የሚገኙ የዞን 9 የጡመራ ቡድን አባላትንና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን በመጠየቅ የዘመቻውን አካል አከናውነዋል፡፡ ቀጥሎም የጥቂት እስረኞችን መልዕክት በአጭር በአጭሩ አቅርበናል፡፡
kiliminto jail
ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ
‹‹ሀገሬ ላይ እርግጠኛ የሆንሁበት ጉዳይ ቢኖር እኔን እንደ ዜጋ የሚጠብቀኝ መንግስት የሌለኝ መሆኑን ነው፡፡ ህገ-መንግስቱ አልጠበቀኝም፡፡ ህገ-መንግስቱ ጥሩ ቢሆንም አልተከበረም፡፡ ይህ ሁሌም የሚያሳዝነኝ ጉዳይ ነው፡፡
ታስሬ ባለሁባቸው ቀናት ሁሉ የታዘብኩት ነገር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የባለሙያ እጥረት በሁሉም ዘርፍ መኖሩን ነው፡፡ አቅም ያላቸው ዜጎች ከስርዓቱ በመገፋታቸው ክፍተቱ እንዲሰፋ ሆኗል፡፡ በጣም ነው የሚያሳዝነው፤ የሚሰሩ ሰዎች በተገቢው ቦታ ላይ አለመኖራቸውን አይቻለሁ፡፡ የሚያሰራ ስርዓት ስለሌለ ብዙዎች ህሊናቸውን መርጠው በመራቃቸው ይመስለኛል አቅም ያላቸው ሰዎች የራቁት፡፡ ይህ ለሀገር አሳሳቢ ነው፡፡
የሚቆጨኝ ነገር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ተቋማት በእንግሊዝኛ የተሰሩ የጥናት ስራዎችን በመምረጥ አሰባስበን በአማርኛ ቋንቋ በጆርናል መልክ ለመስራት አስበን ያን ሳንሰራ በመታሰራችን ነው፡፡
አሁን በተለያዩ ሁኔታዎችና ጉዳዮች ላይ ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያው በኩል የሚሰሩ ስራዎች እንዳሉ ስሰማ በጣም ነው ደስ ያለኝ፡፡ እኛን አስረው ሌላው ዝም እንዲል ፈልገው ኖሮ ከሆነ እንዳልተሳካላቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ለሀገር የሚያስቡ ብዙ ወጣቶች በየጊዜው ማበባቸው አይቀሬ ነው፡፡ እየታየ ያለውም ይሄው ነው፡፡ ምንግዜም የሚበረቱ ሰዎች ለውጥ ያመጣሉ ብዬ አምናለሁ፡፡››
አይመዲን ጀበል፣ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል
ልትጠይቁን ስለመጣችሁ በጣም እናመሰግናለን፡፡ በተለይ ወጣቶቹ እያደረጋችሁ ያለው እንቅስቃሴ እንሰማለን፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡ እስካሁን በአገር ጉዳይ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ የቆዩት የ1960ው ትውልድ አባላት ናቸው፡፡ አሁን ወጣቶች እንቅስቃሴ እያደረጉ ነው፡፡ ይህ ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡ ነገር ግን በቂ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ስለሆነም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡
ያሲን ኑሩ፣ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል
‹‹እስር፣ እንግልትና ሌሎችም በደሎች የአምባገነኖች እርምጃ መለያ ባህሪያት ናቸው፡፡ አምባገነኖችን አንድ የሚያደርጓቸው እነዚህ ባህሪያት ናቸው፡፡ አምባገነኖች ከታሪክ አይማሩም፡፡ የዛሬ 20 አመትም ሆነ 50 አመት ወደ ስልጣን የሚወጣ አምባገነን ይህን ነው የሚደግመው፡፡
መንግስት በኃይማኖቶች መካከል ልዩነት መፍጠር ይፈልጋል፡፡ እናንተ ክርስቲያኖች የኃይማኖት ድንበር ጥሳችሁ ከእኛ ከሙስሊም ወንድሞቻችሁ ጋር መቆማችሁን እናደንቃለን፡፡ በተለይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ መብት በመቆም የሚያደርገውን ጥረት እናደንቃለን፡፡ እኛን ለመጠየቅ እስር ቤት ድረስ ስለመጣችሁ በጣም እናመሰግናለን፡፡ ትግሉ ከዚህም በላይ መስዋዕትነት ያስከፍላልና በርቱ፡፡››
ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ
‹‹ማዕከላዊ የገባነውን የመጀመሪያ ሰሞን ለእኛ አስቸጋሪ ነበር፡፡ በማንኛውም ጊዜ እስር ሊኖር ይችላል በሚል ማዕከላዊ የሚደረጉትን ነገሮች ለማሳወቅ እንጥራለን፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የጻፍናቸው ጽሁፎች ለዚህ ያግዛሉ ብየ አምናለሁ፡፡ በመሆኑም በእኛ ላይ ከደረሱብን ነገሮች ሌሎች ይማሩባቸዋለን ብለን እናምናለን፡፡ ይህ ሲሆን የሚታሰሩ ሰዎች የሚደርስበት ችግር አዲስ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ ወደ ቂሊንጦ ከመጣን በኋላ የተሻለ ነገር ቢኖርም አሁንም ድረስ መጽሃፍና ጋዜጣ አይባልንም፡፡
በጥቁሩ ሳምንት ዘመቻ ያደረጋችሁትን ነገር ሰምተናል፡፡ በጣም ደስ የሚል ስራ ሰርታችኋል፡፡ መጥታችሁ ስለጠየቃችሁን ደስ ብሎናል፡፡ እስሩ ቀጣይነት እንደሚኖረው ቢታወቅም፣ በየትኛውም ሁኔታ በርታትችሁ እንድትቀጥሉ እፈልጋለሁ፡፡
በየቀኑ ጋዜጠኞች በሚደርስባቸው ጫና አገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን እንሰማለን፡፡ ይህ በጣም ያሳዝናል፡፡››
ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ
‹‹ከመታሰሬ በፊት ማዕከላዊ ውስጥ ስለሚፈጸሙ በደሎች በተለያዩ ሪፖርቶች ላይ ማንበብ ችዬ ነበር፡፡ ማዕከላዊ ከገባሁ በኋላ ያየሁት ግን ሰፊና ከጠበኩት በላይ ነው፡፡ በተለይ ትጥቅ ትግልን የመረጡ ተቃዋሚዎች አባላት ናቸው የተባሉ አሊያም በሚዲያው የማይታወቁና ጠያቂ የሌላቸው አካላት ላይ የሚደርሰው በደል ዘግናኝ ነው፡፡ በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ተመሳሳይ ድብደባ ደርሶባቸዋል፡፡ ድሮ ማዕከላዊ ውስጥ ይደረጉ እንደነበር ሰምቼ ነገር ግን ይሆናሉ ብዬ የማላምናቸውን ነገሮች ሁሉ እንደሚፈጸሙ ለመገንዘብ ችያለሁ፡፡
የማዕከላዊ መርማሪዎች አስቸጋሪዎች ናቸው፡፡ ምርመራ ማድረግ ሳይሆን ጥፋተኛ መሆናችንን እንድናምንላቸው ነው ሁሌም ተመሳሳይ ጥያቄ የሚያነሱልን፡፡ አንዳንዶቹ ጥያቄዎች በጣም የሚገርሙ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ያህል በምርመራ ወቅት ‹‹እከሌ ጋር ሻይ እየጠጣን›› ብለን የተናገርነውን ነገር እነሱ ‹‹ስብሰባ አድርገን›› ብለው ይጽፉታል፡፡ ሻይ መጠጣት በእነሱ ስብሰባ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ አንድ ጋዜጠኛ የሚሰራው ህጋዊ ስራ ህገወጥ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ለአብነት ያህል ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25/2004 ዓ.ም ባደረገው ሰልፍ ተገኝቼ ፎቶ አንስቼ ነበር፡፡ ይህ ፎቶ ግራፍ በክስ ቀርቦብኛል፡፡ አስቡት በዚህ ሰልፍ ኢቲቪና ሌሎች የመንግስት ሚዲያዎችም ፎቶ አንስተዋል፣ ቪዲዮ ቀርጸዋል፡፡ መርማሪዎቹን ‹‹ይህ ስራዬ ነው፡፡ አያስወነጅለኝም›› ብትል አያምኑልህም፡፡ ጋዜጠኛ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስም ሰማያዊ ፓርቲ ባዘጋጀው ሰልፍ ላይ ተገኝተሃል የሚል ጥያቄ ቀርቦለታል፡፡
በተመሳሳይ ዩጋንዳ እያለሁ ባቋቋምኩት ጋዜጣ ላይ ሙሃመድ ሰልማን ‹‹ፒያሳ ሙሃመድ ጋ ጠብቂኝ›› በሚል ከጻፈው መጽሃፍ ላይ ያሉ ጽሁፎችን ጋዜጣው ላይ አውጥቻቸው ነበር፡፡ ሆኖም ይህም በክስ ቀርቦብኛል፡፡ ‹‹መጽሃፍ ላይ ነው የወሰድኩት፡፡ መጽሃፉ ህጋዊ ሆኖ አገር ውስጥ ይሸጣል›› ብትል ማንም አይሰማህም፡፡ ፖሊስ ህዝብን ለመጠበቅ የቆመ አካል ተደርጎ ነው የሚወሰደው፡፡ ነገር ግን ከገባንበት ጊዜ ጀምሮ ገና ሳይፈረድብን ‹‹እናንተስ ለምን ሽብር ትፈጥራላችሁ?›› ያሉን ፖሊሶች አጋጥመውናል፡፡ ቀድመው ፈረዱብን ማለት ነው፡፡
በምርመራ ወቅት በጣም የሚያስገርሙ ነገሮች ተነስተዋል፡፡ ለምሳሌ ያህል ጆን ኬሪ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ ወቅት መርማሪዎቹ የሚገርም ጥያቄ አንስተውልን ነበር፡፡ ‹‹ጆን ኬሪ ጓደኛችሁ ነው?›› ብለው ጠይቀውናል፡፡ በጣም የሚገርም ነው፡፡ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣን የእኛ ጓደኛ እንደሆነ አድርገው አቅርበውታል፡፡ ደግሞም ይህንንም ህገወጥ አድርገው ነው የሚያቀርቡት፡፡ በሌላ በኩል አንዴ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር፣ ሌላ ጊዜ ከግንቦት ሰባት ሌላ ጊዜ ደግሞ ከኦነግ ጋር ግንኙነት እንዳለን ይገልጹልናል፡፡ እነዚህ ድርጅቶች በምንም መልኩ የሚገናኙ አይደሉም፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ጋዜጠኛ የሚከሰሰው በመጻፉ አይደለም፡፡ በጋዜጠኝነት ብትከሰስ አንድ ነገር ነው፡፡ እነሱ ግን የሚያነሱብህ ክስ ሌላ ነው፡፡
ፌስቡክና ሌሎች ሚዲያዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ የነበርን ሰዎች ያለመረጃ ስንቀመጥ ከባድ ነው፡፡ በተለይ በመጀመሪያዎቹ 75 ቀናት ነገሮች አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ከዛ በኋላ ግን ቢያንስ ኢቲቪን መመልከት ችለናል፡፡ ኢቲቪ በሚያቀርባቸው ጉዳዮች ላይ የየራሳችን ትርጉም እየሰጠን አገራችን ውስጥ በጥቂቱም ቢሆን ምን እየተካሄደ እንዳለ መረዳት እንችላለን፡፡ ወደ ቂሊንጦ ከመጣን በኋላ ነገሮች የተሻሉ ናቸው፡፡ ከጠያቂዎቻችን መረጃዎችን ማግኘት እንችላለን፡፡››
ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

tirsdag 9. september 2014

የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት 400 ሰዎች በተገደሉበት የጋምቤላ ጭፍጨፋ የሕወሓት ባለስልጣናት መሳተፋቸውን አጋለጡ

የቀድሞው የጋምቤላ መሪ በክልሉ ለደረሰው ጭፍጨፋ የህወሃት ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረጋቸውን ኢሳት ዘገበ። የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ኦሞት ኦባንግ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ 400 ሰዎች የተገደሉበት የጋምቤላው ጭፍጨፋ እንዴት እንደተከናወነ በዝርዝር ሁሉን ነገር ተናግረዋል።
omot obang
እንደ ኦሞት ገለጻ የህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አባይ ፀሐዬ ግድያውን በተመለከተ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል ያሉ ሲሆን በክልሉ ስለሚፈጸመው ሙስናና የመሬት ወረራ የቀድሞው ባለስልጣን በዝርዝር በዝርዝር ተናግረዋል።
የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ኦሞድ ወደ ውጭ ከወጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሰጡት በተነገረው በዚህ ቃለምልልሳቸው ላይ 400 ሰዎች በግፍ በአባይ ፀሐዬ ከፍተኛ ሚና መገደላቸውን መዘርዘራቸው ወደፊት በነዚህ ባለስልጣናት ላይ ለሚከፈተው ክስ ጥሩ ምስክር ሊሆን ይችላል ተብሏል።

mandag 8. september 2014

በአዲስ አበባ በየሰፈሩ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች “ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው በሚል ወከባ ይደርስባናል” አሉ

Dish addis ababaአዲስ አበባ ውስጥ በየ ቤቱ እየዞሩ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው›› በሚል ወከባ እንደሚደርስባቸው ገለጹ፡፡ ወጣቶቹ ከኢሳት ውጭ ያሉ ጣቢያዎች የሚተላለፉበት ዲሽ በሚገጥሙበት ወቅትም ‹‹ኢሳትን እየቀጠላችሁ ነው፡፡ ህዝቡ ኢሳትን እንዲያይ ታደርጋላችሁ›› በሚል በደህንነቶች ወከባ እንደሚደርስባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡
በተመሳሳይ ከወራት በፊት መርካቶ አካባቢ ዲሽ የሚገጥሙ ወጣቶች ‹‹ኢሳትን ለህዝቡ እያሳያችሁ ነው›› ተብለው በፖሊስ ተይዘው እንደነበር ተጠቁሟል፡፡ ያም ሆኖ ግን በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ኢሳትን እንደሚገጥሙ የሚያሳዩ የዲሽ ማስታወቂያዎች ይታያሉ፡፡ ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ


ብኵርና በቀይ ወጥ እንደዘበት !

ብኵርና በቀይ ወጥ እንደዘበት !

Sept 7, 2014

 ይድነቃቸው ከበደ

ኤሳው ከእናቱ መኋፀን ቀድሞ በመወለዱ ብቻ ሣይሆን ከፈጣሪው የተሰጠው ልዩ ፀጋ ነበረው፡፡ግን ኤሳው ለጢቂት ጊዜ ቢርበውም መታገስ አቅቶት ለታናሽ ወንዱሙ ብኵርናውን በቀይ ወጥ ለወጠ፡፡ሆኖም ግን በልቶ ሲጠግብ ብኵርናውን ቢፈልጋት ከእርሱ ተለይታለች፡፡ኋላም ለንስሐ ህይወት እድል ሳያገኝ ሞተ፡፡ ዘፍ.25 ቁ 5-33 ፡፡ ብኵርና ወይም ታላቅነት የእድሜ ብቻ ሣይሆን የፀጋም ጭምር ነው፡፡ፀጋ ደግሞ እድሜ፣ ሀብት፣የሰው ፍቅር፣አርቆ አስታዋይነት እና የመሣሰሉት ሁሉ የሚያካትት ነው፡፡
ከላይ በጢቂቱ ተገልፆ የሚገኘው ከመፃህፍ ቅዱስ የተወሰድ ሃሳብ ነው፡፡ሆኖም ግን የአገራች ወቅታዊ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ህዝባዊ አመኔታ ባጣው በገዥው በወያኔ መንግስት የህዝብ ፍቅር እና ዝና በቀይ ወጥ ስለሚለውጡ ታዋቂ ሰዎች በወፍ በረር ለመዳሰስ ነው፡፡እንደሚታወቀው አገራችን ኢትዮጵያ የታዋቂ ሰው ችግር አለባት ለማለት የሚያስችል ምንም አይነት አስተማማኝ መረጃም ሆነ ማስራጃ ማግኘት የማይቻል ነው ፡፡ ሆኖም ግን አሉን የምንላቸው ከራሣቸው ጥረት ባለፍ የፈጣሪ ፀጋ ታክሎበት በህዝብ ዘንድ እውቅናን ያተረፉ ለቁጥር ያልበዙ እውቅ ሰዎች ስለመኖራቸው ማንም የማይክደው ሃቅ ነው፡፡
በመሆኑም ከተገፋው ጋር እየተገፉ ለአገር እና ለወገን ቅድሚያ እየሰጡ በክብር ላይ ክብር እያገኙ በሰው ልብ ውስጥ በፍቅር የሚኖሩ ምርጥ ኢትዮጵያዊያን እውቅ ሰዎች አሉን፡፡ እነዚህ እውቅ ሰዎች እውቅና ያተረፉበት መንገድ እና ሙያ የተለያየ ቢሆንም አንድ የሚያደርጋቸው እውቅናቸውን በቀይ ወጥ አለመለወጣቸው ነው፡፡ቀይ ወጥ ደግሞ ሌላ ምንም አይደለም የለየለት አድር ባይነት ነው፡፡የአድር ባይነት መሠረቱ ደግሞ ሐሰት ነው፡፡አሉን የምንላቸው አዋቂ ሰዎች ግን ሐሰት ከሆነ ሣይሆን እውነት ከሆነው ጎኖ መቆማቸው ነው፡፡
እውነት የሆነው ነገር ደግሞ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ቤት የሚገኝ የውስጥ እግር ቁስል ነው፡፡ እሱም ከአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ በመነሣት በመንግሰት የአስተዳደር ብሉሹነት ምክንያት እየደረሰብን ያለ በደል ነው፡፡በደሎ ደግሞ እራብ፣ስደት፣ስራ-አጥነት፣የመብራት እና የውሃ እጥረት፣የዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች መረገጠ፣ እና ከመኖሪያ ቦታ መፈናቀል እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ሌላው እና አሳሳቢው ነገር የአምልኮ ቦታዎች በልማት ስም ይፈርሳሉ፣ የእምነት አባቶች እና መምህራኖች  ይታሰራሉ እንዲሁም ይሰዳዳሉ፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ቤተ-ክርስቲን እና መስጂዶች የገዥው መንግሰት የፖለቲካ ማራመጃ ተቋም ሆኗአል፡፡
እነዚህን ችግሮች በመለየት እና በአግባቡ በመረዳት አማራጭ መፍትሔ ለማምጣት እና ብሉሹ የሆነው የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ተደራጅቶ በፖለቲካ ፓርቲ መንቀሳቀስ አስቸጋሪ የሆነበት ወቅት ልይ ነው የምንገኘው፡፡ መንቀሳቀስ ሲባል ምርጫ ቦርድ እና መንግስት ቀለብ ሰፍሩላቸው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎችን የሚመለከት አይደለም፡፡በመሆኑም ቁጥሩ እየጨመር የሚሄድ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኛ መብዛቱ፣በታሳሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይ እና በደል እጅግ በጣም የበዛ ነው፡፡
ስለዚህም እነዚህን እና መሰል ችግሮችን ለመጠቆም እና ለማወያየት እንዲሁም መፍትሔ ለማመላከት ነፃ ሚዲያ ያለው አስታውፆኦ ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ይሁን እንጂ በአገራችን እንደነዚህ አይነት ጋዜጠኞች ይታሰራሉ ወይም እንዲሰደዱ ይደረጋል፡፡ መንግሰት ከፍተኛ ባጃት በመመደብ ጠንካራ የሚዲያ ተቋማትም በውጪ እንዲሁም በአገር ውስጥ ያሉ  እንዲፈርሱ ወይም እንዲታፈኑ ያደርጋል፡፡ይህ ነው እንግዲ የአገራችን ወቅታዊ እውነት የሆነው ነገር !
ይሁን እንጂ እነዚህ እና መሰል ግፍ እና በደሎችን በመንግስት ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ እየተፈፀመ ይገኛል፡፡ሆኖም ግን ይህን አይቶ እንዳላየ ማልፍ በራሱ አንድ ነገር ሆኖ እያለ፤ምንም ቢሆን ከመጠየቅ ባያድንም፡፡ ይበልጥ ግን የሚያስቆጨው እና የሚያንገበግበው ለእንዲህ አይነቱ መከራ እና ስቃይ የሚዳርገውን መንግስት መደገፍ እና ለመጥፎ ተግባሩ መስክር በመሆን ዘብ በመቆም አድር ባይ ሲኵሆን ማየት ምን የሚሉት እብደት ነው ! ብሎ ማለት ምኑ ላይ ነው ስህተቱ ?
ጥያቄው በራሱ ስእተት ባይሆንም በስእተት ሳይሆን በድፍረት ላዛውም እንደዘበት፡፡ የህዝብ ፍቅር እና ዝና በርካሽ ነገር አላፊ ጠፊ በሆነ፤ ስም እና ዝናቸውን እየለወጡ ፈራሽ የሆነውን መንግሰት በመተማመን በህዝብ ላይ የሚቀልዱ የታዋቂ ሰዎች የቁልቁለት ጉዞ በርክቷል፡፡ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ አስተዛዛቢ ድርጊት ሣይፈፅሙ ወይም ሣይቃወሙ መኖራቸው በራሱ የሚያሳጣቸው ነገር የለም፡፡ይሁን እንጂ  ደሃ ከበዛበት የአገራችን ኑሮ መቶ እጥፍ እየኖሩ መቶ እጥፍ ከእነሱ አንሱ በሚገኝ በድሃ ህዝብ ላይ መከራውን ከሚያበዛው የህዝብ ውክልና ከሌለው፣ የመንግስትነትን ስም ይዞ ከሚንቀሳቀስ የአንድ አካባቢ ተወላጅ ስብስብ ጋር በማበር ከህዝብ ዘንድ ያገኙትን ብኵርና በቀይ ወጥ የለወጡ ስኖቶች ናቸው ?
ቀን አይለወጥ መስሏቸው ማንነታቸውን በርካሽ ነገር የለወጡ እና ለመለወጥ ያሰቡ የመመለሻቸው ጊዜ አሁን ነው፡፡እጅ የሰጡለት ወደቃዊ መንግሰት እጅ መንሳቱ አይቀሪ ነው፡፡እሱም ቢሆን ወዶ ሳይሆን በግዱ ነው! ያኔ ግን እንደዘበት ያጡት ብኵርና ከወዴትም አይገኝም፡፡