søndag 6. april 2014

በደሴ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ


April 6, 2014
UDJ party demonstration in Dese
አንድነት ፓርቲ “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ መፈክር በተለያዩ ከተሞች የሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግ ባሳወቀው መሰረት ዛሬ በደሴ ከተማ ብዙ ሺህ ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ድምጹን ሲያሰማ ውሏል።
በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ከተስተጋቡት መፈክሮች ውስጥ ጥቂቶቹ፣
- መሬት ከካድሬው ወደ ህዝቡ ይመለስ
- አንድነት ኃይል ነው
- የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ
- መሬት ለህዝብ ይመለስ
- ጭቆና በቃን
- ድል የህዝብ ነው
- በግፍ የታሰሩ ይፈቱ
በሰላማዊ ሰልፉ ማብቂያ ላይ የአንድነት ፓርቲ ተ/ም/ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ፣ የአንድነት ፓርቲ ውጪ ጉዳይ ኃላፊ ኢ/ር ዘለቀ ረዲ እንዲሁም የአንድነት ፓርቲ የደሴ ሰብሳቢ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያ ሳይሸበር አደባባይ ወጥቶ ድምጹን ያሰማውን የደሴና አካባቢውን ህዝብ አመስግነዋል።

Ingen kommentarer:

Legg inn en kommentar