የሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 17 ቀን 2005 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት ፅ/ቤት ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጥሪ ባስተላለፈው መሰረት አመራሮቹ ዝግጅት በማድረግ ላይ እንደሆኑ ገለጹ።
ይህ በዚህ እንዳለ በፌስቡክ፣ ፓልቶክና ሌሎችም የማህበራዊ መገናኛ መረብ (social media) ተጠቃሚ ኢትዮጵያውያን ለተጠራው የሰላማዊ ሰልፍ ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። በርካታ ኢትዮጵያውያን የፌስቡክ ፎቶዎቻቸውን በጥቁር የሰው ምስል በመቀየር ድጋፋቸውን እያሳዩ ሲሆን የፓልቶክ መወያያ መድረክ ታዳሚዎች ደግሞ ጽሁፎቻቸውን በጥቁር ቀለም በመቀየር ሰማያዊ ፓርቲ ጥቁር ልበሱ ሲል ያስተላለፈውን መልዕክት ተግባራዊ እያደረጉ ነው።
እስካሁን ከገዢው ፓርቲ አካባቢ የተጠራውን የሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የተባለ ነገር የለም።
የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት ሰላማዊ ሰልፈኞች ቀደም ብለው ስለ ሰላማዊ ሰልፋቸው እንዲያሳውቁ የሚደነግግ ሲሆን። የግድ ፈቃድ መጠየቅ እና ማስፈቀድ አለባቸው አይልም።
Ingen kommentarer:
Legg inn en kommentar