søndag 22. juni 2014

ፀረ ሙስና ኮሚሽን የምድር ባቡር የድሬዳዋ ኃላፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋለ

112የፌደራሉ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የቀድሞ የኢትዮ-ጂቡቲ ምድር ባቡር ኩባንያ የድሬዳዋ ተጠሪንና አራት ሌሎች የአመራር አባላትን፣ በሙስና ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ሥር አዋለ፡፡
ከድሬዳዋ በተገኘ መረጃ መሠረት ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት የቀድሞው ዋና ተጠሪ አቶ አየለ ወልደ ዮሐንስ፣ የሐዲድና የሕንፃ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ገበየሁ፣ የሳብ ተሳሳብ ኃላፊ የነበሩት አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም፣ የአኬሌ ወርክሾፕ ኃላፊ አቶ ፍቅረ ማርያም አበባየሁና የንግድና ትራንስፖርት ተጠሪ የነበሩት አቶ ደርብ ጉደታ መሆናቸው ታውቋል፡፡
አቶ አየለን ጨምሮ አምስቱም ተጠርጣሪዎች በድሬዳዋ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀርበዋል፡፡ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ሥልጣንን ያላግባብ በመጠቀም፣ የመንግሥትን ይዞታ ለግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በማከራየትና የመንግሥት የግዢ ሥርዓት ሳይጠብቁ ግዢ በመፈጸም ክስ መመሥረቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ባለፈው ሚያዝያ ወር በተመሳሳይ የድሬዳዋ ፖሊስና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ፖሊስ በጋራ በመሆን የኢትዮ ጂቡቲ ምድር ባቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩትን አቶ ጣዕመ ተኪኤን፣ ጉቦ በመቀበል ወንጀል በድሬዳዋ ከተማ ውስጥ ባረፉበት ሆቴል በቁጥጥር ሥራ ማዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ከአሥር ወራት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያጡ የፍቼ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሠልፍ ሊወጡ ነው

ካህናትና የነዋሪዎች ተወካዮች ዋና መሥሪያ ቤቱን ተማፀኑ
819f5b6eb52350a170986a3670177bfb_Lላለፉት አሥር ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ኩራዝ ብርሃን ለመመለስ ተገደናል ያሉ በኦሮሚያ ክልል የፍቼ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች፣ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ለከተማው አስተዳደር ጥያቄ ማቅረባቸውን አስታወቁ፡፡
ነዋሪዎቹ ሠልፍ እንደሚወጡ የከተማውን አስተዳደር መጠየቃቸውን የገለጹት፣ ነዋሪዎቹን ወክለውና የከተማውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት አባቶችን ልብሰ ተክህኖ በመልበስና ሌሎች የሃይማኖት ተወካዮች እንደእምነታቸው ለብሰው፣ ፒያሳ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ተገኝተው ቅሬታቸውን ባሰሙበት ወቅት ነው፡፡
የፍቼ ከተማ ነዋሪዎች ላለፉት አሥር ወራት የኤሌክትሪክ ኃይል አጥተው መክረማቸውን የመሥሪያ ቤቱ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት እማኝ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ ከፍቼ እስከ አዲስ አበባ ከተማ ያሉትን ቢሮዎች ቢያዳርሱም፣ አንዱ ወደ ሌላኛው ቢሮ እንዲሄዱ ከመንገር ባለፈ የፈየዱላቸው እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ብሶታቸው እየባሰ በመምጣቱና ከመንግሥት አንድ ቁርጥ ያለ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው በማመናቸው፣ ሁሉንም የከተማውን ነዋሪዎች በመወከል ከ25 የሚበልጡ ተወካዮች በዋናው መሥሪያ ቤት ተገኝተው ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡
‹‹ጥያቄያችን የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ ነው፤›› ያሉት ነዋሪዎቹ፣ ለብዙ ጊዜያት በኤሌክትሪክ ኃይል መጠቀም የለመዱ ነዋሪዎች እንደገና ወደኋላ በመመለስ በኩራዝና በማገዶ እንዲጠቀሙ ማድረግ ተገቢ አለመሆኑንና በተለይ በዕድሜ የገፉ እናቶችና ጨቅላ ሕፃናት ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም የሚመለከተው የመንግሥት አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ በመሥሪያ ቤቱ የተለመደው ምላሽ ‹‹ትራንስፎርመር አልተገዛምና የለም›› መሆኑ ማብቃት ስላለበት መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት መስጫ መሥሪያ ቤት አንድ ኃላፊ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹ሁለት ሰው ይበቃ ነበር፣ ብዙ በመሆናችሁ ቅር ብሎኛል፡፡ እኛ እናንተን ማገልገል እንጂ ሌላ ዓላማ የለንም፡፡ ከእኛ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት አንድ ሰውና ከእናንተ አንድ ሰው ይበቃ ነበር፡፡ ወይም በወረቀት ደብዳቤ ብትጽፉም በቂ ነበር፡፡ ሁለተኛ እንዳይደገም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ችግሩን አጣርተው መፍትሔ ምላሽ እንደሚሰጡም ተናግረዋል፡፡
እንደ ፍቼ ነዋሪዎች ለአሥር ወራት የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል መጥፋት ችግር ባያጋጥምም፣ ከአምስት ቀናት እስከ አንድ ወር ድረስ የኃይል መጥፋት ችግር የሚያጋጥማቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም በተለያየ መንገድ እሮሮ እያሰሙ ነው፡፡ አዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍላተ ከተሞች በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል እየጠፋ እንደሆነ ራሱ መሥሪያ ቤቱ ምስክር እንደሚሆን፣ እንደማይጠራጠሩ ስድስት ኪሎ የካቲት 12 ሆስፒታል አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ትዕግሥት በላቸው በእርግጠኝነት ይናገራሉ፡፡
ወ/ሮ ትዕግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል በተከታታይ ለአራት ቀናት ካልጠፋ ‹‹የዓባይ ግድብ ደረሰ መሰለኝ፣ ተመስገን ያለምንም ችግር ጨለማ ሳይውጠን ከረምን፤›› እስከማለት መደረሱን ተናግረዋል፡፡
ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል እስከ ሾላ ገበያ ድረስ ያሉ ነዋሪዎች ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት የኤሌክትሪክ ኃይል በማጣታቸው ‹‹የዓለም ዋንጫ ለኛ ሲባል ሊደገም ነው አሉ…›› እያሉ በችግሩ ላይ ማሾፍ መጀመራቸውንም ወ/ሮ ትዕግሥት አንድ ዘመዳቸውን ለመጠየቅ በሄዱበት ወቅት መታዘባቸውን ጠቁመዋል፡፡
እንደነ ወ/ሮ ትዕግሥት አካባቢ ሁሉ በሽሮሜዳ፣ በፒያሳ፣ በሜክሲኮ፣ በቃሊቲ፣ በአቃቂ፣ በጎተራ፣ በቦሌ፣ በኮተቤ፣ በአስኮ፣ በላፍቶ፣ በልደታና በሌሎች አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ጉዳይ አነጋጋሪ ብቻ ሳይሆን ጥያቄም እያስነሳ መሆኑን ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት መከፈሉ ይፋ ከተደረገ አንድ ዓመት ሳይሞላው እየተፈጠሩ ያሉት ችግሮች፣ ነዋሪዎችን ግራ እንዳጋቡ የሚገልጹ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጠው ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይስ ከእኛ ከገዙት ጁቡቲና ሱዳንም?›› በማለት ጥያቄ እያሰኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ሁለት ቦታ ተከፍሎ የሠራተኞች ምደባ እንደ አዲስ መደረጉ ለችግሩ ዋና ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ በተለይ የአገልግሎት ዘርፉን የተረከበው የህንዱ ኩባንያ ሥራውን በአግባቡ እየተወጣው አለመሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ነባር ሠራተኞች ሥራውን በደንብ የሚያውቁት ቢሆንም፣ በተደረገው አዲስ የመዋቅር ለውጥ ድልድል ሳያኮርፉ እንዳልቀሩ የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎች፣ የሚመለከተው አካል ይኼንን ሁኔታ በደንብ አጥንቶ አስቸኳይ መፍትሔ ካልሰጠው፣ ችግሩ የከፋና ውጤቱም አደገኛ እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል፡፡ የአገልግሎት ዘርፉን ከሚመራው የህንዱ ኩባንያ ጋር የሥርጭት ዘርፉን በኃላፊነት የሚመሩት የሥርጭት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢትወደድ ገብረ አሊፍን ለማነጋገር ቢሞከርም ስልካቸውን ስለማያነሱ አልተሳካም፡፡

lørdag 21. juni 2014

ፖሊስ በሐዋሳ ከተማ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላትን በሙሉ አሰረ- የታሰሩትንም ደህንነት ማወቅ አልተቻለም

ፖሊስ በሐዋሳ ከተማ በቅሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላትን በሙሉ አሰረ
1050አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በነገው እለት ማለትም ሰኔ 15/2006 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በራሪ ወረቀት በማደል ፤ ፖስተር በመለጠፍና በሞንታርቦ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ የአንድነት አባላትን በሙሉ አስሯል፡፡ በሞንታርቦ ቅስቀሳ ላይ የነበሩት የነበሩ የአንድነት ፓርቲ አባላትን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመሀል ክ/ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡
አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)በነገው እለት በሀዋሳ ሀተማ ለሚያደርገውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ፖስተር በመለጠፍ፡በራሪ ወረቀት በማደልና በሞንታርቦ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ የነበሩ የፓርቲው አባላት በፖሊስ ተይዘው በተለያዩ በከተማዋ ፖሊስ ጣቢያዊች የሚገኙ ቢሆንም ማንም እንዳይጠይቃቸው በመደረጉ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ አልተቻለም፡፡የሀዋሳ ከተማ ከተማ ፖሊስ መምርያ የመሀል ክ/ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ሀላፊ ስማቸውን መግለፅ እንደማይፈልጉና ማንም መጠየቅ እንደማይችል እንዲሁም መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ኮሚሽነርን ስለሁኔታው ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡

በእስር ላይ የሚገኙት አባላት የሞባይል ስልካቸውን ተቀሙ
1048974አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በነገው እለት ማለትም ሰኔ 15/2006 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የሚያካሂደውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በቅስቀሳ ላይ እንዳሉ በፖሊስ ተይዘው የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመሀል ክ/ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት እንዲሁም በባህል አዳራሽ ፖሊስ ጣቢያ በእስር ላይ የሚገኙ የአንድነት አባላት ከማንም ጋር እንዳይገናኙ የሞባይል ስልካቸውን ተቀሙ፡፡ከስልካቸው በተጨማሪም በራሪ ወረቀቶቻቸውን ፖሊስ በሀይል ቀምተዋል፡፡
10464338_655647427853528_5549276093091202318_n10390200_655645774520360_6136971251416251946_n10487183_655644054520532_1488061453046983959_n\
1041
10
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

fredag 20. juni 2014

The Simplest Step Ethiopians Can Take to Protect Themselves From Excessive Gov’t Surveillance

June 20, 2014

by Jessica McKenzie
Tech President
The Ethiopian government has at their disposal a formidable collection of surveillance technologies, and can intrusively monitor writers and activists at home and abroad. In late April the government arrested six independent bloggers and a journalist. More than 50 days later they are still being held in custody, and yet no formal charges have been filed. In March Human Rights Watch published a lengthy and detailed report warning that surveillance in Ethiopia could get even worse if the government gains the human capacity necessary to fully leverage the available technologies.The Ethiopian government has at their disposal a formidable collection of surveillance technologies
One of the most invasive and potentially life-threatening things that can happen to an Ethiopian blogger, journalist, activist or dissident is to unwittingly download malware that allows the government to monitor keystrokes and passwords, to remotely turn on a computer’s microphone or camera and start recording, and to extract data from the hard drive. The simplest step Ethiopians can take to protect themselves is to limit the number of documents they download from the Internet. One way to do this is by opening documents as Google Docs.
Until recently, however, Google Docs did not support the Ethiopian language Amharic. Now that they do (and it seems a simple and easy thing to add), Ethiopians have a powerful tool with which to protect themselves from unlawful and intrusive government surveillance.
The Electronic Frontier Foundation has an excellent post explaining how to enable Amharic in Google products, and why Ethiopians should use it (namely, if they are worried about their own government’s surveillance but not concerned that Google will supply their data to US court orders).
I have previously written for techPresident about Angolan investigative journalist Rafael Marques, who discovered intrusive malware on his computer with help from hacker and activist Jacob Appelbaum. Months after the discovery Marques was arrested and beaten.
One of the most relevant points Marques makes is that the malware doesn’t need to be sophisticated because the authorities know or anticipate that he does not have the resources to buy a new, clean computer and to thoroughly protect it.
Is the Google Doc trick infallible? Almost certainly not, but it is a free, easy way for Ethiopians to protect themselves. Think of it like wearing a seatbelt in cyberspace.

በሃዋሳ 3 የአንድነት አመራርና አባላት ታሰሩ – “እስሩ ቅስቀሳውን አያስተጓጉለውም”

newsአንድነት ፓርቲ እሁድ ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት” በሚል መሪ ቃል በሃዋሳ ከተማ ለሚደረገው የተቃውሞ ሰልፍ በራሪ ወረቀት በማደልና ፖስተር በመለጠፍ ላይ የነበሩት የአንድነት ፓርቲ አመራርና አባላት ታሰሩ፡፡ ሲዳማ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ሲዳ ኃይሌ እንዲሁም ከማዕከል ለሰልፉ እገዛ ለማድረግ ከሄዱ የፓርቲው አባላት መካከል አቶ ኃይሉ ግዛውና ወጣት ደረጄ ጣሰው ላይ ህገወጥ እስር መፈፀሙን ከስፍራው ለፍኖተ ነፃነት የደረሰው መረጃ አመላክቷል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ ባለስልጣናት ሰልፉን ለማደናቀፍ የሚያደርጉት የተቀነባበረ እንቅስቃሴ ያልበገራቸው ሌሎቹ የቅስቀሳ ቡድኑ አባላት የተጠናከረ ቅስቀሳ ለማድረግ መዘጋጀታቸው ታውቋል፡፡
ምንጭ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ
ራሳችንን ነጻ እናዉጣ ፤ ሰኔ 15 ቀን አዋሳ እንገናኝ
- አማኑኤል ዘሰላም
የደቡብ ክልል ዋና ከተማ ናት። በርካታ ብሄረሰቦች በፍቅር የሚኖሩባት ዉብ ከተማ። ሰኔ 15 ቀን 2006 ዓ.ም ደሴን፣ ባህር ዳርን፣ አዳማን፣ ጊዶሌን አዲስ አበባ እና ደብረ ማርቆስን በመቀላቀል ድምጿን ታሰማለች። አዋሳ !!!!
የሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትሕና ለመሬት ባላቤትነት በሚል መርህ በሐዋሳ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል። ለሰልፉ የከተማዋ ባለስልጣናት እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ የአንድነት አባላትን ደጋፊዎች ቅስቀሳ ጀምረዋል።
የሰላማዊ ትግል ቁልፍ ሥራ ትግሉን ወደ ሕዝቡ ማዉረድ ነው። የሚሊዮኖች እንቅስቃሴም እያደረገ ያለው ይሄንኑ ነው። ይሄን ሰልፍ ለማድረግ የታሰበው ከአንድ ወር በፊት የነበረ ቢሆንም የአገዛዙ ባለስልጣናት የተለያዩ ምክንያቶች እየሰጡ ሰልፉን እስከአሁን እንዲዘገይ አድርገዉት ቆይተዋል። በዞኑ የአንድነት አመራር አባላት ባሳዩት ትእግስትና ቁርጠኝነት ሰልፉ እዉቅ አግኝቶ ቅስቀሳ ተጀምሯል።
በሚቆጣጠራቸው የመገነኛ ብዙሃን ለሕዝብና ለአገር መልካም እንዳደረገ፣ ለሕግ የበላይነትና እንደቆመ፣ ሁሉንም በእኩል እንደሚያይ ኢሕአዴግ ይለፍፋል። «ኢሕአዴግ ለአዋሳ ሕዝብ ጥቅም የቆመና ሕዝቡን የሚያከብር ነው ወይ ? ባለስልጣናቱ ህዝቡን የሚያሰቃዩና የሚያንገላቱ ሳይሆን በቅንነት ሕዝብን ያገለግላሉ ወይ ? » የሚሉ ጥያቄዎች ቢነሱ መልሱ «አይደለም» የሚል እንደሆነ የአዋሳ ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮያ ሕዝብ ያውቀዋል።
ኢሕአዴጎች የሚኩራሩበትና ግፍ ሲሰሩ ምንም የማይከብዳቸው «ሕዝቡ ፈሪ ነው ፤ ድምጹን ማሰማት አይደፍርም። ከኛ ፍቃና ትእዛዝ ዉጭ አይወጣም» የሚል እምነት ስላላቸው ነው። የአዋሳ ህዝብ ኢሕአዴጎች እንደሚያስቡት ሳይሆን፣ መብቱን፣ ነጻነቱን፣ ክብሩን አሳልፎ የማይሰጥ ህዝብ መሆኑን የሚያሳይበት ሰልፍ ተዘጋጅቷል። የኣዋሳ ህዝብ »እምቢ ለአምባገነንት፣ እምቢ ለዘረኝነት፣ እምቢ ለሙስና ፣ እምቢ ለፍትህ መጓደል፣ እምቢ ለኑሮ ዉድነት … » የሚልበት ሰልፍ የሚደረግበት ቀን እንሆ ደርሷል። ሰኔ 15 !!!!!
አገር ነጻ የምትሆነው፣ ክልሎች ነጻ ሲሆኑ ነው። ክልሎች ነጻ የሚሆኑት ወረዳዎች ነጻ ሲሆኑ ነው። ወረዳዎች ነጻ የሚሆኑት ቀበሌዎች ነጻ ሲሆኑ ነው። ቀበሌዎች ነጻ የሚሆኑት ቤተሰብ ነጻ ሲሆን ነው። ቤተሰብ ነጻ የሚሆነው እያንዳንዳችን በግልሰብ ደረጃ ነጻ ስንሆን ነው። በግላችን «ለመብቴ መቆም አለብኝ። እስለመቼ ባሪያ ሆኜ፣ አቅርቅሬ እኖራለሁ» በማለት ለራሳችን ፣ በግላችን ነጻነትን ስናወጅ ፣ ያኔ ከሌሎች ጋር ሆነ የነጻነትን ደዉል ለመደወል አይከብደንም።
እንግዲህ የነጻነትን መልእክት ለራሳችን እናስተላልፍ። ዛሬ እኛ በራሳችን አይምሮ ዉስጥ ፈቅደን ካስቀመጥነው ፍርሃትና የሕሊና መሽመድመድ ነጻ እንዉጣ። አዋሳ የምንኖር ሰኔ 15 ቀን የሚደረገዉን ሰልፍ እንቀላቀል። ከአዋሳ ዉጭ ያለን በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የምንኖር ወገኖች በአዋሳ ያሉ ዘመድ፣ ወዳጆቻችንን በስልክ፣ በኢሜል፣ በቫይበር ፣ በቴክስት በማግኘት ሰልፉን እንዲቀላቀሉ እናበረታታ። በሶሻል ሜዲያ፣ በራዲዮኖችና ድህረ ገጾችም በፓልቶኮች ቅስቀሳዉን እናፋፍም። በገንዘብ ድጋፍ እናድርግ። በአካል ባንገኝም በመንፈስ ሰልፉን እንቀላቀል።
ይህ የአንድ ሰው፣ ወይንም የአንድ ፓርቲ ንቅናቄ አይደለም። ይህ የሚሊዮኖች ንቅናቄ ነው። ይህ የሕዝብ ትግል ነው። በመሆኑም የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ተሳትፎ ያስፈልጋል። እያንዳንዳችን የድርሻችንን ለመወጣት እንዘጋጅ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን ። አዋሳ በአካልም ይሁን በመንፈስ እንገናኝ !

ቀና ብለን የምንሄድበት ጊዜ አየመጣ ነው! ጎበዝ ተነሳ!

June 20, 2014
ጉጅሌዎቹ አይገባቸውም እንጂ የኢትዮጵያ ከተሞችና ገጠሮች የለውጥን |ደመና ኣርግዘዋል። ወንዞችም ተራሮችም የለውጥ ማዕበል ማቆብቆቡን አያበሰሩ ናቸው። የቀደሙት ገዢዎች መረጃ የሚያገኙት እረኛ ምን ይላል ብለዉ እየጠየቁ ነበር። የአሁኖቹ አገር አጥፊ ገዢዎች ምሳሌ ያደረጉት ካድሬዎቻቸውን ብቻ ሆነ እንጂ ዛሬም የአገራችን እረኞች የለውጥን መምጣት በሚያምር ቅላጽያቸው አያንጎራጎሩ እንዲህ አያሉን ነው፣
የሀገሬ ጉብል የሰማውን እንጃ
የጎንደሬው ጉብል የሰማውን እንጃ
ከብቱን አየሸጠ ገዛ ኣሉ ጠብመንጃ።
የወለጋው ጉብል የሰማውን እንጃ
ቡናውን ሻሽጦ ገዛ ኣሉ ጠብመንጃ።
መልእክቱ ግልጽ ነው። የኢትዮጵያ ወጣቶች አገራቸውን በክቡር ደማቸው ሊታደጓት ቆርጠው በመነሳት ወያኔን በማስወገድ የሀገራቸው ባለቤት ለመሆንና ያልተከፋፈለች ውብ ኢትዮጵያን ማየትን ለማረጋገጥ ጥርጊያውን መጀመራቸው ነው።
ላለፉት ፵ አመታት አምባገነኖች ባደረሱብን ጭቆና እና እንግልት የተነሳ የራሳችን የሆነ መንግሥት ሳይኖረን አንገታችንን ደፍተን ጀግኖቻችንን ስንገብር ኖረናል። በተለይም ባለፉት ፪፫ አመታት ጉጅሌዎቹ በአራት ኪሎ ከነገብን ጀምሮ በአንድ ላይ አንዳንቆም በማድረግና እና አርስ በራሳችን በማጋጨት ሲያባሉን ኖረዋል።
ዛሬ ሁኔታዎች ተለውጠዋል፤ በውጭም በአገር ውስጥም ለውጥ አየታየ ነው። የእንቅስቃሴው ማእበል አይሎ እየመጣ ነው። ዛሬ ሁሉም የዴሞክራሲ ሀይሎች ማለት በሚቻል ደረጃ በሁለት ነገሮች ላይ ስምምነት አለ፣
፩. ተቃዋሚዎች በግል ከሚያደርጉት ትግል ይልቅ በጋራ የመሰባሰብን አስፈላጊነት ተረድትው መሰባሰብ መጀመራቸው
፪. በአንድ ላይ መሰባሰብ ካልቻሉም እርስ በራስ ላለመጠላለፍ መስማማት መቻላቸውና አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ግዜ ሁሉ መረዳዳት መጀመራቸውና በግልም ከወያኔ ጋር የሚደረገውን ትግል ማፋፋም የቻሉበት ሁኔታ አየታየ መሆኑ የሕዝብ ወገኖችን እያስደሰተ ይገኛል።
በአገር ቤት የሚገኙ የዴሞክራሲ ኃይሎችም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ሕዝቡ ከፍርሀት ተላቆ ለመብቱ አንዲነሳ የሚያደርጓቸው አንቅስቃሴዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከሩ መጥተዋል። ለዚህም በቅርቡ በአዲስ ኣበባ መድረክ፣ ኣንድነትና ሰማያዊ ፓርቲዎች የጠሯቸው ሰልፎች ይበል የሚያስብሉ ናቸው።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ በዚሀ ኣጋጣሚ ለዴሞክራሲና ለነፃነት ታጋዮች ሁሉ ያለውን አክብሮትና ኣድናቆት ይገልጻል።
በሌላም በተለያዩ አቅጣጫዎች ወያኔን በኣመጽ ለመፋለም የወሰኑ ኃይሎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ወያኔን ለመፋለም ቆርጠው በጋራ ክንዳቸውን ኣቀናጅተው ለመፋለም አየተዘጋጁ ያሉበት ሁኔታ አበራታች ነው። እነዚህ ኃይሎች አዳዲስ የነጻነት ታጋይ አርበኞችን በተከታታይ በማስመረቅ ያሉ መሆናቸውና ከዚህም በተጨማሪ ከመላው የአገሪቱ አካባቢዎች ወጣቶች በገፍ ትግሉን እየተቀላቀሉ መሆኑን ስንሰማ ልባችን በደስታ ይሞላል።
በወያኔ ጉያ ውስጥ ያሉ የሕዝብ ወገኖች ደግሞ የቻሉትን በውስጥ ሆነው መቃብሩን እይቆፈሩለት ሲሆን፣ ያልቻሉትም የወያኔን ሚስጢር ይዘው በመውጣት የሕዝብ ወገንተኝነታቸውን አየገለጹ ይገኛሉ።
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ለመላው ሕዝባችንና በተለይም ለወጣቱ ትውልድ በተደጋጋሚ አንደሚለው የሀገራችን ባለቤት ለመሆን የምናደርገውን ትግል ተቀላቀሉ!!! መቀላቀል ያልቻላችሁም በኣካባቢያችሁ ከምታምኗቸው ወገኖቻችሁ ጋር ተሰባሰቡ፣ በህዋስ ተደራጁ። ግንቦት 7 በዚህ ትግል የዳር ተመልካች ሳይሆን መሪ እንድትሆኑ ኣገራዊ ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

torsdag 19. juni 2014

Zone 9 journalists & bloggers among 2014 EHSNA honorees

For Immediate Release – 
Honorees of the Fourth Ethiopian Heritage Festival
Poet Laureate, Young Scholar and Journalists to be honored:
• An Ethiopian Poet Tsegaye Gebremedhin will be honored for his Contribution to the Advancement of Humanity
• The Zone Nine bloggers: Free press Journalist for reporting the truth, corruption, and the human rights condition in Ethiopia at great personal sacrifice and risk.
• Nahom Marie, a 17 Years old, software and iOS app developer who will be attending MIT.
These are among those who will be primarily honored, celebrated, and remembered at the upcoming Ethiopian Heritage Fourth annual Festival to be held from Friday, July 25 to 27th 2014.
Laureate Tsegaye “Giant” and “Icon”
Poet Laureate Tsegaye Gebremedhin was a renaissance man. He was poet, playwright, essayist, historiographer, philologist, art director, humanist, and peace activist. Born in 1936 Ambo, Ethiopia, Tsegaye Gebremedhin’s artistic talent was noticed early on by his grade school teacher. Into adulthood, he advanced to become a prolific playwright and poet. Throughout his life time, he has published over 11 research papers, over 40 plays and poetry in Amharic, and translated more than 16 plays in Amharic and English, some being his work.
Moreover, he has also held several positions such as was General Manager of the Ethiopian National Theatre, Vice-Minister of Culture and Sports, editor at the office of Oxford University Press, assistant professor at department of Education at Addis Ababa university from (1977-1978) and much more. His awards include the following: Emperor Haile-Selassie I International Prize for Amharic Literature in 1966, The Gold Mercury Ad Persona Award in 1982, 4 Fulbright Senior Scholar Resident Fellowship Award; Human Rights Watch Free Expression Award in New York in 1994, and Honorable Poets Laureate Golden Laurel Award. In addition, his literary contribution particularly to Ethiopia is immense and remains as an icon etched not only in Ethiopian history and identity, but to Africans as well.
BmSkWVxCIAADXux-300x154
Unsung Heroes- Zone9 bloggers
Zone9bloggers are a group of bloggers dedicated to presenting the various pertinent social issues such as political repression and human rights activism. The six bloggers are Atnaf Berahane, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Befeqadu Hailu, Zelalem Kiberet, Abel Wabela, and 3 journalists; Edom Kassaye, Tesfalem Weldeyes and Asmamaw Hailegorgis of Addis Guday magazine. After much surveillance and harassment, as of April 26th they have been charged with terrorism and imprisoned at Maeklawi prison which is notorious for torture. The ESHNA acknowledges the diligent work zone9bloggers have contributed to human rights and the idea of free expression.
Young scholar- Nahom Marie
nahom_marieNahom Marie is a bright 17 years old high school student whose academic achievement is exemplary. Nahom’s exceptional academic began whilst in Kindergarten where he exhibited a higher understand that advanced him to several classes beyond his age.
Nahom Marie is an aspiring software and iOS app developer from San Jose, California. He has worked on different types of apps from BOOM, a music recognition app that utilizes the capabilities of the Pebble smart watch, to an in-progress tutoring app that looks to make the process of tutoring and/or finding a tutor tailored to compatibility and several preferences.
Graduating this summer, Nahom has received several awards and scholarships to various universities such as Princeton, Sanford, Harvard, MIT and many more. Besides his academic achievement, he has engaged himself in working within the Ethiopian community. He often volunteered after school to help students with their homework’s, and acting not only as their tutor but as mentor as well.

Ethiopian Heritage Festival to be an Interesting Event
Along with the ceremonial honorees, the Ethiopian Heritage Festival will offer venues for members of the Ethiopian Diaspora Community and their American neighbors to learn about and celebrate the Ethiopian experience. These include art, crafts, and jewelry exhibitions. Plenty of delicious Ethiopian cuisine, traditional music and dancing, soccer and running sports, and plenty of activities for the youngsters will keep everybody interested.
Main days of the Ethiopian Heritage Festival: Opening Friday, July 25 at Silver Spring Civic building 1 Veterans Pl, Silver Spring, MD 20910 and Saturday July 26 through Sunday, July 27, 2014, on the campus of Georgetown University in Washington, D.C
For more info please visit our website www.ehsna.org
Or email us @-pr@ehsna.org
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.